Ethiopians life in cape town

Ethiopians life in cape town መረጃ የፍትህ ደምጽ በዚህ ሚዲያ ላይ እናቀርባለን ይህ ፔጅ መቀመጫው ደቡብ አፍሪካ ስሆን ጠቅላለ በአለም ዙሪያ ያለውን መረጀውችን የምያከትት ስሆን ለሁልም አግልግሎቶች መልዕክቶች መጠቅም ይቻላል!!!

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 118.9 ቢሊየን ብር ገቢና 20.25 ቢሊየን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን አስታወቀየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት (2025/26) 118.9...
07/08/2026

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 118.9 ቢሊየን ብር ገቢና 20.25 ቢሊየን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት (2025/26) 118.9 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ገቢ በማስመዝገብ ከያዘው ዕቅድ 102.6 በመቶ ማሳካቱን አስታውቋል። ተቋሙ በዚሁ ዓመት 20.25 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱም ተገልጿል።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፣ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ከገቢ አሰባሰብ ጀምሮ እስከ ትርፍ ድረስ የሚታይ እመርታ ማሳየቱን ገልጸዋል።

በታክስ ክፍያም ተቋሙ ለመንግሥት 12.39 ቢሊየን ብር መክፈሉን የገለጹት ኢንጅነሩ፣ ይህ አፈጻጸም ከ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ56 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት 664 ሺህ 505 አዳዲስ የኤሌክትሪክ ደንበኞችን ማፍራቱን ገልጿል። በዚህም 205 የገጠር ከተሞች ለመጀመሪያ ጊዜ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል።

ኢንጅነር ጌቱ ገረመው እንዳሉት፣ በተለያዩ አካባቢዎች አልፎ አልፎ የሚያጋጥሙ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጦችን ለመቀነስ ሰፊ የኔትወርክ ማሻሻያና የመሠረተ ልማት ሥራዎች መከናወናቸውንም አስረድተዋል።

ተከሳሽ ወ/ት ኢክራም አማን ገቲሶን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ በከፈተቻቸው ሶስት የተለያዩ የባንክ ሂሳቦች ውስጥ በአጠቃላይ 30,840,490.99 ገቢ እንደተደረገላት በምርመ...
07/08/2026

ተከሳሽ ወ/ት ኢክራም አማን ገቲሶን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ በከፈተቻቸው ሶስት የተለያዩ የባንክ ሂሳቦች ውስጥ በአጠቃላይ 30,840,490.99 ገቢ እንደተደረገላት በምርመራ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

ወ/ት ኢክራም አማን በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ ከተመሰረተው ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ መዝገብ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋለች ተጠርጣሪ ናት።

የተከሳሽ አቶ ነቢል አንዋር የቅርብ ሰው እንደሆነች የተነገረላት ተጠርጣሪዋ ለአቶ ብርሃኑ አለቃ፣ ለአቶ ኤርሚያስ ተክሉ እና ለአቶ ነቢል አንዋር ከተለያዩ አካላት የሚሰበሰበውን የሙስና ገንዘብ በመቀበል እና በደላላነት ቀጥተኛ ተሳትፎ እንደነበራት ታውቋል።

ከማህበረሰቡ ወግና ባህል እንዲሁም እምነት ያፈነገጡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ ።(ባምባሲ ከተማ ፖሊስ፣ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም) ከማህበረሰቡ ወግና ...
07/08/2026

ከማህበረሰቡ ወግና ባህል እንዲሁም እምነት ያፈነገጡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ ።

(ባምባሲ ከተማ ፖሊስ፣ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም) ከማህበረሰቡ ወግና ባህል እንዲሁም እምነት ያፈነገጡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ ።

በፎቶ የተመላከቱት እኒሁ ታደለ እናውጋውና በፀሎት እንየው የተባሉ ተጠርጣሪዎች በተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ በመመስረታቸው በማህበረሰቡ ጥቆማና ተጠርጣሪዎቹም የእምነት ቃላቸውን በሰጡት መሰረት ፖሊስ ተገቢውን የምርመራ ስራ መጀመሩንና በቀጣይ ውጤቱን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን ።

📢 ወንጀልን በጋራ እንከላከል‼️

ወቅታዊና ሚዛናዊ መረጃዎችን ቀድሞ እንዲደርሳችሁና ለሌሎችም ተደራሽ እንዲሆን
#ሼር
#ፎሎው
#ላይክ በማድረግ አብራችሁን ሁኑ
እንቀበላለን

መርሐችን


የባምባሲ ከተማ አስ/ር ፖሊስ መምሪያ
ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም

06/08/2026

Once white man say
I will talk only 30 second with you!!! What funny man

እናት እያለቀሰች፣ ልጅ አደባባይ ላይ እርቃኗን...🤔🤔 የኢትዮጵያዊነት ሞራል ወዴት እያመራ ነው❓❓ሰሞኑን በቲክቶክ መንደር እያየነው ያለው ነገር በእጅጉ ልብ ይሰብራል፣ ያሳፍራልም። አንዲት ...
05/08/2026

እናት እያለቀሰች፣ ልጅ አደባባይ ላይ እርቃኗን...🤔🤔 የኢትዮጵያዊነት ሞራል ወዴት እያመራ ነው❓❓

ሰሞኑን በቲክቶክ መንደር እያየነው ያለው ነገር በእጅጉ ልብ ይሰብራል፣ ያሳፍራልም። አንዲት በአሜሪካ የምትኖር ኢትዮጵያዊት ወጣት በቲክቶክ ላይቭ ላይ ገብታ የምታሳየው እጅግ አሳዛኝ፣ ክብረ ነክ እና ማንነታችንን የማይወክል ድርጊት ብዙዎቻችንን አስደንግጧል። ወጣቷ እራሷን በማዋረድ፣ ከእኛ ባህልና እሴት ባፈነገጠ መልኩ አደባባይ ላይ ስትታይ፤ ከድርጊቷ በላይ ደግሞ ልብ የሚያደማው እዛው ላይቭ ላይ ያሉ አንዳንድ አዋቂ ነን ባዮች እና ወንዶች "ጎበዝ፣ ቀጥይበት" እያሉ ሲያጨበጭቡላት ማየታችን ነው። ተይ፣ ይህ መንገድ አያዋጣም፣ ስህተት ነው ብሎ ከመገሰፅና ከመምከር ይልቅ፣ ለራሳቸው መዝናኛ ሲሉ እርኩሰትን ማበረታታቸው የዘመኑን የሞራል ውድቀት በግልፅ ያሳየናል።

ከሁሉም በላይ ደግሞ አንጀት የሚበላው እና የሰማውን ሁሉ እንባ የሚያስመጣው የድሃ እናቷ ለቅሶ ነው። እናትየዋ ስኳር በሽተኛ ሆና፣ ራሷን እየጎዳች በቀን ለ16 ሰዓታት በከባድ ድካም እየሰራች፣ ስንት መከራና ስቃይ አይታ ልጇን ወደ አሜሪካ ያመጣችው የተሻለ ህይወት እንድትኖር አስባ ነበር። ዛሬ ግን ያቺ የለፋችላት ልጅ በሶሻል ሚዲያ ላይ በምታሳየው አሳፋሪ ተግባር ምክንያት እናትየዋ በህዝብ ፊት እያነባች ትገኛለች። "እግዚአብሔር ለምን ወንድ ልጅ አልሰጠኝም?" ብላ በምሬት እና በፀፀት ስታለቅስ መስማት የትኛውንም ሰብዓዊ ፍጡር፣ በተለይም እናት የሆነችን ሁሉ ልብ የሚሰነጥቅ ነው። እናት ስንት ለፋች፣ ውጤቱ ግን የህዝብ መሳቂያ መሆን ሆነ።

እውነት ቲክቶክ ትውልድ ማጥፊያ እየሆነ ነው ወይስ እኛው ራሳችን ነን አጠቃቀሙን ያበላሸነው? አንዳንዶች ይህቺን ወጣት ከመምከር ይልቅ ለላይክ፣ ለቪው እና ለተከታይ ብዛት ሲሉ ብቻ ሲያሾፉባትና ሲጠቀሙባት ማየት እጅግ ያሳዝናል። አንዲት አስተዋይ እህት ላይቭ ላይ ገብታ ወንዶቹን "ይህንን እኩይ ድርጊት እንዴት ታበረታታላችሁ? እናንተስ ልጅ የላችሁም?" ብላ ስትሞግታቸው ታይታለች፤ ይህቺ እህት ትልቅ ምስጋና ይገባታል። በስህተት መንገድ ላይ ያለን ሰው መገሰፅ፣ መምከር እና ወደ ትክክለኛው መንገድ መመለስ የሁላችንም ኃላፊነት መሆን ሲገባው፣ በማጨብጨብ ገደል እንድንገፋው መፍቀድ የለብንም።

ይህቺ ልጅ ምናልባትም የአእምሮ፣ የስነ-ልቦና ወይም የከፋ ጭንቀት ውስጥ ልትሆን ትችላለች። ስለዚህ ማፌዝና ማሾፍ አቁመን ልንረዳት፣ እንዲሁም ሪፖርት አድርገን አካውንቷን በማዘጋት ከዚህ የጥፋት መንገድ ልንታደጋት ይገባል። በዛው አሜሪካ እና አካባቢው ያላችሁ ወገኖችም እናትየዋን ብታፈላልጉ፣ ብታፅናኑና ከጎኗ ብትሆኑ ትልቅ በጎነት ነው። ዛሬ በሰው ልጅ ላይ የደረሰው ነገ በእኛ ቤት እንደማይደገም ማንም ዋስትና የለውም።

ልጆቻችንን እና ትውልዱን ከእንደዚህ አይነት የሶሻል ሚዲያ ማዕበል እና አደጋ በጋራ እንታደግ! 🙏
ፈጣሪ ለእናቷ ብርታትን ይስጥልን። 😭

(መረጃው የአሃዱ ሚዲያ ነው)

በ‘YBS Market’ አማካኝነት ከፍተኛ የትርፍ ክፍያ እናስገኛለን በሚል ሽፋን ከበርካታ ዜጎች በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሰበሰበው የግል ድርጅት መስራች ወልደጊዮርጊስ፣ ላለፉት ሁለት ቀና...
05/08/2026

በ‘YBS Market’ አማካኝነት ከፍተኛ የትርፍ ክፍያ እናስገኛለን በሚል ሽፋን ከበርካታ ዜጎች በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሰበሰበው የግል ድርጅት መስራች ወልደጊዮርጊስ፣ ላለፉት ሁለት ቀናት ሙሉ በሙሉ ምላሽ ባለመስጠቱ ኢንቬስተሮች በከፍተኛ ስጋትና ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ።
ድርጅቱ በየወሩ ከፍተኛ ትርፍ እንደሚከፍልና ከስድስት ወራት በኋላ ደግሞ የተቀመጠውን ዋና ገንዘብ ይመልሳል በሚል በተሰጠ የተስፋ ቃል፣ በርካታ አዲስ አበቤዎች የመኖሪያ ቤቶቻቸውንና መኪኖቻቸውን በመሸጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር ኢንቨስት ማድረጋቸው ይታወቃል።
በኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከተከሰቱት ተመሳሳይ የገንዘብ ማጭበርበር አጋጣሚዎችና አሁናዊ ሁኔታዎች አንጻር፣ እስከ 20 እና 30 ሚሊዮን ብር ድረስ መድበው በድርጅቱ ውስጥ ያስገቡ ባለሀብቶችና ግለሰቦች ሁኔታው ከቁጥጥር ውጭ እንዳይሆን በከፍተኛ ስጋት ላይ ይገኛሉ። ላለፉት 48 ሰዓታት ከወልደጊዮርጊስም ሆነ ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ይፋዊ መግለጫ ወይም የሁኔታዎች ማብራሪያ አለመሰጠቱ ኢንቬስተሮችን ግራ አጋብቷል።
በርካታ ኢንቬስተሮች በ YBS Market ቢሮዎችና በስልክ መስመሮች በኩል መረጃ ለማግኘትና ያለበትን ለማወቅ ጥረት ቢያደርጉም እስካሁን ምንም አጥጋቢ ምላሽ ማግኘት አልቻሉም።
ይህ ሁኔታ በተለይ ንብረታቸውን ለውጠውና ዕዳ ገብተው የተሳተፉ ኢንቬስተሮችን ለከፍተኛ የስነ-ልቦና እና የኢኮኖሚ ጫና የዳረገ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትና የሕግ አስከባሪዎች ጉዳዩን በአስቸኳይ ትኩረት ሰጥተው እንዲከታተሉት ጥሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።

      SamiDaily7 follow this page
05/08/2026

SamiDaily7 follow this page

አሳዘኝ ክስታት  SamiDaily7
03/08/2026

አሳዘኝ ክስታት SamiDaily7

ከእስር በ800ሺህ ዋስ ተለቆል
03/08/2026

ከእስር በ800ሺህ ዋስ ተለቆል

መንሱር ጀማል ከእስር ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቀሉ::

በፊንቴክ ጉዳይ ተጠርጥረው በእስር ላይ የነበሩት መንሱር ጀማል፣ የተወሰነባቸውን የ800 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘብ ባለፈው አርብ ዕለት ገቢ በማድረጋቸው ሙሉ በሙሉ ከእስር ተለቀዋል።

ለ«ጉርሻ ፔጅ» በደረሰውና በተረጋገጠው መረጃ መሠረት፣ መንሱር ጀማል የዋስትና ሂደታቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው በአሁኑ ሰዓት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።

03/08/2026

SamiDaily7 follow for more news

Address

Cape Town

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopians life in cape town posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopians life in cape town:

Shortcuts

Share