Sodo and Arbaminch DHL Branch

Sodo and Arbaminch DHL Branch Excellence, Simply Delivered

20/03/2026
12/03/2026

"በክልሉ ጋሞ ዞን በተለያዩ አከባቢዎች በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ እስከ አሁን የ70 ሰዎች ህይወት አልፏል"፦ የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት

ዎላይታ ሶዶ፣መጋቢት 3/2018 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)

በአደጋው ከመኖሪያ ቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ጊዜያዊ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር በዘላቂነት ለማቋቋም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም ተመላክቷል

የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ ኃይለማሪያም ተስፋዬ አደጋውን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

የጋዜጣዊ መግለጫ ዋና ዓላማ በአደጋው የደረሰውን ጉዳት ለማሳወቅና የሠብዓዊ ድጋፍ ለማሰባሰብ ያለመ መሆኑም በመግለጫው ተጠቁሟል።

የአገልግሎቱ ኃላፊ እንደገለፁት መጋቢት 01/2018 ዓ.ም በጋሞ የተለያዩ አከባቢዎች በጣለው ከባድ ዝናብ በ4 ወረዳዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

አደጋው 3 ሺህ 480 የቤተሰብ ዓባላት ያሉዋቸው 575 አባወራና እማወራዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ማፈናቀሉንም የአገልግሎቱ ኃላፊ አቶ ኃይለማሪያም አብራርተዋል።

በዞኑ በተከሰተው አደጋ 190 የመኖሪያ ቤቶች የወደሙ ሲሆን እስከ ቀኑ 8 ሰዓት ድረስ የ70 ሰዎች አስከሬን መገኘቱንም ጠቁመዋል።

በተያያዘም በአርባ ምንጭ ከተማ የኩልፎ ወንዝ በመሙላት ተፈጥሮአዊ አቅጣጫውን ለቆ በመሄድ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ 31 በተለያዩ ደረጃ የሚገኙ ማህበራት፣ 2 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችና 1 የግብረ ሰናይ ድርጅት ንብረት ውድሟል።

የክልሉ መንግስት በጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ እንዲሁም የጤና አገልግሎት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም አቶ ኃይለማሪያም ገልፀዋል።

በቀጣይ 10 ቀናት ዝናቡ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሜትሮሎጂ ትንበያ ይገልፃል ያሉት የአገልግሎቱ ኃላፊ በስጋት አከባቢዎች የሚገኙ ዜጎች አከባቢውን እንዲለቁ የማድረግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

አደጋውን አስመልክቶ የአይነት ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ ተቋማትና ግለሰቦች አርባምንጭ ከተማ በመምጣት የጋሞ ዞን አስተዳደርን ሊያገኙ እንደሚገባ የገለፁት አቶ ኃይለማርያም የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ 1000321312865 የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት ጽ/ቤት በሚል የሂሳብ ቁጥር እንዲያስገቡ አሳስበዋል።

ህብረተሰቡ በአደጋው ህይወታቸው ያጡ ወገኖችን ፎቶና የቪዲዮ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከመልቀቅ ሊቆጠብ ይገባል ያሉት አቶ ኃይለማሪያም ትክክለኛ መረጃዎችን ብቻ ሊከታተል እንደሚገባም አሳስበዋል።

በአደጋው ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ ጉዳት መድረሱን ያወሱት ኃላፊው በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ምክር ቤት በጋሞ ዞን እና አርባ ምንጭ ከተማ በተከሰተ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ ፈጣን ምላሽ መስጠት በሚቻልበት ዙሪያ በመምከር የተለያዩ አቅጣጫዎች ማስቀመጡንም አቶኃይለማሪያም ተስፋዬ በሰጡት ጋዜጣዊ በመግለጫ አስታውቀዋል።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u
ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

12/03/2026

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በጋሞ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለጹ

| የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ማዞ ዶይሳ ቀበሌ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት ናዳ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖችና ጉዳት ለደረሰባቸው ቤተሰቦች ያላቸውን አጋርነት ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን በመግለጽ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውም መጽናናትን ተመኝተዋል።

በአካባቢው የተከሰተው ይህ አደጋ በርካታ ቤተሰቦችን ለሃዘንና ለችግር የዳረገ ሲሆን፣ ድርጅቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ሰብአዊ ድጋፍ ለማቅረብ ቁርጠኝነቱን አረጋግጧል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

#ጌጡ

12/03/2026
😥😥😥
12/03/2026

😥😥😥

የአድራሻ ለውጥውድ ደንበኞቻችን የ DHL ቢሯችንን ወደ ጦና ህንፃ መቀየራችንን በአክብሮት እናሳውቃለን::በተጨማሪ ለአዲስ አመት እና ጊፋታ በተደረገው ታላቅ ቅናሽ ተጠቃሚ ይሁኑ::የበዐል አል...
13/07/2025

የአድራሻ ለውጥ
ውድ ደንበኞቻችን የ DHL ቢሯችንን ወደ ጦና ህንፃ መቀየራችንን በአክብሮት እናሳውቃለን::
በተጨማሪ ለአዲስ አመት እና ጊፋታ በተደረገው ታላቅ ቅናሽ ተጠቃሚ ይሁኑ::
የበዐል አልባሳት የተዘጋጁ ምግቦች የ ተለያዩ ስጦታዎች ይላኩ በራቸውን አንኳክተን በፍጥነት እና ታማኝነት እናደርስሎታለን::
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር
0912244415
0910821172
ይደውሉ::

18/02/2025
17/02/2025
Take your local market to Global market.Use DHL and Simlly become exporters.
17/02/2025

Take your local market to Global market.Use DHL and Simlly become exporters.

Address

S**o

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:00
Tuesday 08:30 - 17:00
Wednesday 08:30 - 17:00
Thursday 08:30 - 17:00
Friday 08:30 - 17:00
Saturday 08:30 - 12:30

Telephone

+251944423151

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sodo and Arbaminch DHL Branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sodo and Arbaminch DHL Branch:

Share