Karat Zurya Woreda Science & Information Technology

Karat Zurya Woreda Science & Information Technology Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Karat Zurya Woreda Science & Information Technology, Konso.

‎ በአዲሱ መዋቅር አደረጃጀት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነዉ የተሾሙት አቶ ኩቱቶ ኩሲያ ቀድሞ የጽ/ቤቱ  ኃላፊ ተወካይ ከነበሩት ከአቶ ደስታ ደምሳሹ  ጋር የስራ ርክክብ  አድርገ...
19/11/2025

‎ በአዲሱ መዋቅር አደረጃጀት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነዉ የተሾሙት አቶ ኩቱቶ ኩሲያ ቀድሞ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ተወካይ ከነበሩት ከአቶ ደስታ ደምሳሹ ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል ።

ቀድሞ የነበሩ የሥራ ኃላፊ በአድስና በሽግሽግ ለመጡ ተሿሚ መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸዉ ተመኝተዋል።

‎መረጃ፦‎የካራት ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ነው።

‎ ህዳር 10/032018 ዓ/ም

በካራት ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቭስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በአስፈፃሚ መ/ቤቶች አደረጃጀትና ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሪ ትግበራ ላይ ለአስፈፃሚ አካላት የተዘጋጀዉ ወረዳዊ የኦሬንተሽን መድረክ...
31/10/2025

በካራት ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቭስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በአስፈፃሚ መ/ቤቶች አደረጃጀትና ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሪ ትግበራ ላይ ለአስፈፃሚ አካላት የተዘጋጀዉ ወረዳዊ የኦሬንተሽን መድረክ ተጠናቀቀ

‎በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳዉ ምክትል አስተዳዳሪና የትም/ት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኩሻቦ ኩሴ ይህ የአስፈፃሚ መ/ቤቶችን መልሶ ማደራጀት ትግበራ ለሁለት ዓመታት ሲደረግ የቆየ ጥናት ግኝት ውጤት መሆኑን ጠቅሰው፣ የመልሶ ማደራጀቱ ዋና ዓላማ የክልሉን ፀጋ አሟጦ በመጠቀምና አንድነቱን በማጎልበት የብልጽግናን ራዕይ እውን ማድረግ መሆኑን አስገንዝበዋል።

‎በሌላ በኩል አዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ እስኬል ማሻሻያ ፐብሊክ ሰርቫንቱ በኑሮ ውድነት ጫና ከተግባር መነጠሉን ተከትሎ መንግስት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ደመወዝ በመክፈል ሠራተኛውንና ተግባሩን ለማስተሳሰር ያደረገው ጉዳይበመሆኑ አመራሩና የሚመለከታቸው አካላት በደንብና በመመሪያው መሠረት ተፈፃሚ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

‎በተመሳሳይ መልኩም የተቀናጀ የ90 ቀናት የፓርቲና የመንግስት ስራዎችን ዕቅድ በቁርጠኝነት መፈፀም ያስፈልጋል ያሉት አቶ ኩሻቦ፤ በዋናነት የፓርቲ መዋጮን መክፈል፣ አደረጃጀቶችን ማጠናከር እና በንቅናቄ የሚመሩ የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በቁጭት ማከናወን እንደሚገባና በመልሶ ማደራጀት ትግበራ ማግስት ምንም ዓይነት የተልዕኮ መንጠባጠብ ሳይኖር ተግባራት በቁርጠኝነት መከናወን እንዳለባቸው ጠንከር ባለ መልእክት በማስገንዘብ አሳስበዋል።

የመንግስት መስሪያ ቤቶች የደመወዝ ስኬል ማሻሻያ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 134/2018 መሠረት፣
‎በአዲሱ የአስፈፃሚ ተቋማት መዋቅራዊ አደረጃጀት መመሪያ ሰነድ ዙሪያ የወረዳዉ ፐብልክ ሰርቭስና የሰዉ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎዳና ጉይታ ገለፃ አድርገዉ፣

‎በቀረቡት ሰነዶች ላይ ሃሳብና አስተያየት የሰጡ የመድረኩ ተሳታፊዎች አዲሱ የተቋማት አደረጃጀት ለረጅም ጊዜ በጉጉት ሲጠበቅ የቆየና የመንግስትንና የህዝብን ሀብት ከብክነት ለማዳን ከፍተኛ ሚና ያለው ከመሆኑ በተጨማሪ የተቋማት የተልዕኮ ግጭት ችግርን የሚቀርፍ በመሆኑ የመንግስትን እና የፓርቲ ተግባራትን ጠንክረን በመፈፀም ውጤታማ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል።

‎የወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቭስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎዳና ጉይታ አዲሱ መዋቅራዊ አደረጃጀትም ሆነ አዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ የኑሮ ውድነት ጫናን ምክንያት በማድረግ ከመንግስት ስራ የተነጠለ ሠራተኛን ከተግባር ጋር ለማስተሳሰር የተደረገ በመሆኑ ሠራተኛው የስራ ሰዓትን ማክበርን ጨምሮ ለተገልጋዩ ቀልጣፍ አገልግሎት በመስጠት የስራ ዋጋ የሆነውን ደመወዝ ማግኘት እንደሚገባው አሳስበዋል።

‎በማጠቃለያ መድረኩም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት አቶ ኩሻቦ ኩሴ፣ ሁሉም ተቋማት ፣ የአዲሱ መዋቅር አደረጃጀት የወረዳችንን ብልጽግና ከፍ የሚያደርግ በመሆኑ የኦሬንተሽን መድረኮችን እና የግንዛቤ ስራዎችን ወደ ታች መዋቅሮች ማውረድ እንደሚገባ መመሪያ በመስጠት አሳስበዋል።

‌‎መረጃው፦የካራት ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ነዉ።

‎ጥቅምት 20/02/2018 ዓ/ም

ዶክተር ህብረት አታራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኢኖቬሽንና ምርምር ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።‎‎መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ እንመኛለን!!
27/10/2025

ዶክተር ህብረት አታራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኢኖቬሽንና ምርምር ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

‎መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ እንመኛለን!!

‎አቶ ፍረው አድማሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የአይስቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።‎‎መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ እንመኛለ...
27/10/2025

‎አቶ ፍረው አድማሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የአይስቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

‎መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ እንመኛለን!!

ልዩ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ተጀመረጥቅምት 14/2018 ዓ.ም  የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ለሦስት ቀናት የሚቆይ ልዩ የምዝገባ ንቅናቄ በዛሬው ዕለት ጀምሯል፡፡በተቋሙ የምዝገባ ዳ...
24/10/2025

ልዩ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ተጀመረ

ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ለሦስት ቀናት የሚቆይ ልዩ የምዝገባ ንቅናቄ በዛሬው ዕለት ጀምሯል፡፡

በተቋሙ የምዝገባ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሄኖክ ጥላሁን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት፥ ዛሬ የተጀመረው ልዩ ምዝገባ ተመዝጋቢዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ለማምጣት ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡

ልዩ የምዝገባ ንቅናቄው እስከ መጪው እሁድ የሚቀጥል ሲሆን፥ በዋናነትም በትምህርት ዘርፉ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ላይ የሚያተኩር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በዚህም ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎችንና በጠቅላላው የትምህርቱን ማኅበረሰብ በልዩ ምዝገባው በስፋት ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱንም ነው ዳይሬክተሩ የገለጹት፡፡

የብሔራዊ መታወቂያ ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር በስፋት እየተሳሰረ በመሆኑ ኅብረተሰቡ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ይበልጥ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል፡፡

በተለይም በስራ ቀናት ለብሔራዊ መታወቂያ መመዝገብ ያልቻሉ ዜጎችን ታሳቢ በማድረግ የምዝገባ አገልግሎቱ በቀጣዮቹ ሁለት የእረፍት ቀናት በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

የምዝገባ አገልግሎቱ ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ በመደበኛነት ከሚሰጥባቸው የኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ፖስታ ማዕከላት በተጨማሪ በትምህርት ቤቶች ቅጥር ግቢ ጭምር እንደሚሰጥም ነው የገለጹት፡፡

እስካሁን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ26 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ ዜጎች የብሔራዊ መታወቂያ ማግኘታቸውን ጠቅሰው፥ በዚህ በጀት ዓመት መጨረሻ 40 ሚሊየን ዜጎችን ለመመዝገብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ኅብረተሰቡ በተለይም የትምህርቱ ማኅበረሰብ ነገ እና ከነገ በስቲያ ቀጥሎ በሚካሄደው ልዩ ምዝገባ አማካኝነት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑና መምህራንና የትምህርት ቤቶች አመራሮች ተማሪዎችን እንዲያስተባብሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የኤፍ ኤም ሲ መረጃ ያመለክታል።

ዶክተር ቦጋለ ቦሻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሾሙ ‎‎ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም (ኢቴ ቢሮ)‎ዶክተር ቦጋለ ቦሻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖ...
23/10/2025

ዶክተር ቦጋለ ቦሻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሾሙ

‎ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም (ኢቴ ቢሮ)

ዶክተር ቦጋለ ቦሻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

!!

02/10/2025
25/09/2025
25/09/2025
25/09/2025

Address

Konso

Telephone

+251934631495

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Karat Zurya Woreda Science & Information Technology posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Karat Zurya Woreda Science & Information Technology:

Share