10/09/2025
"የነገው ቀንን" ስናስብ አሁን ያለንበትን ቴክኖሎጅ ተቋማት መከተል እንዳለባቸው ለማስገንዘብ በማሰብ ነው።
ጳጉሜ 05 ቀን 2017 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ፅህፈት ቤት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ቡድን "ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" በሚል መሪ ሐሳብ ጳጉሜ 5 ቀን "የነገው ቀንን" ለመንግስት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር አካሄደ።
የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸው ነገሰ በመርሐ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፣ ኢትዮጵያውያን ቀደምት ከምንታወቅበት ስልጣኔ ወጥተን ወደ ኋላ የቆየንበት ጊዜ ቢኖርም አሁን ላይ ዲጂታል ዘርፋን መከተል አለብን።
ተቋማት ከቴክኖሎጅው ጋር መታረቅ ይኖርባቸዋል ያሉ ሲሆን፤ አሁን ያለንበትን የዲጂታል አለም ይዘን የሞያው ባለቤቶች ልንሰራበት ይገባል ብለዋል።
ከቴክኖሎጂው ጋር ለመሄድ ቀኑን አስበን ብንውልም የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ትኩረት ሊያደርጉበት ይገባልም ብለዋል።
በመድረኩ አከባበር ላይ የተገኙት የሰሜን ሸዋ ዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሜሮን አበበ እና የመንግስት ኮሙኑኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተማለደ በላይሁን ስለቴክኖሎጂው ጠቀሜታ አስተያየት በመስጠት የዲጂታል ሽግግር አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ በአቶ ደመላሽ በላይ በበኩላቸው "የነገው ቀን" ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚል ሰነድ ለተሳታፊዎች አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡
ለተሳታፊዎች መጪው ጊዜ የቴክኖሎጂ ነውና ዲጂታል ኢትጵያን እውን ማድረግ የሁላችንም ድርሻ በመሆኑ በፍጥነት የዞናችንን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ይጠበቅብናል ያሉት ቡድን መሪው፤ በመድረኩ የጥያቄና መልስ ውድድር በማድረግ እውቅና በመስጠት የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብሩ ላይ የዞኑ አመራሮችና የመንግስት ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
ዘገባው የ(ሰሸዞመኮ) ነው