አቡራ ሻንጉል ሚዲያ

አቡራ ሻንጉል ሚዲያ Info link

በአሶሳ ዞን ኡንዱሉ ወረዳ ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ እየተካሄደ ነው‎‎‎በመርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት፦ የቤኒሻንጉል ብሐረሰብ ምክር ቤት አፈ ጉ...
03/08/2026

በአሶሳ ዞን ኡንዱሉ ወረዳ ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ እየተካሄደ ነው


‎በመርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት፦ የቤኒሻንጉል ብሐረሰብ ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የዞኑ መስተዳድር ተወካይ አቶ ዑመር አብዱልቃድር እንዳሉት፦ አረንጓዴ አሻራ የጠቅላይ ሚኒስተሩ እንዱ ኢንሸቲቭ መሆኑን ገልጸው።

‎ዛሬ ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ ችግኝ ስንተክል መሪ ቃሉን በመገንዘብ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

‎ችግኝ መተከል ብቻውን ግብ አይደለም ያሉት አቶ ዑመር በተለይ ኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውን ጨምሮ እንደ ልጅ ቆጥሮ በመንከባከብ ለፍሬ ለማብቃት ሁሉም በኃላፊነት ስሜት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።


‎የኡንዱሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታጀዲን አጀሊ እንዳሉት ፦ በዞኑ መሪነት ዛሬ በኡንዱሉ ወረዳ የችግኝ ተከላ መከናወኑመልካም ዕድል መሆኑን ተናግረዋል።

‎ከዚህ ቀደም ላለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች አሁን ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱንም ተናግረዋል።

‎በዘንድሮው የአረንጎዴ አሻራ መርኃ ግብር 300 ሺህ በላይ ልዩ ልዩ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የወረዳው ግብርና ጽህፈት ኃላፊ ሀሊፋ ታጀስር ናቸው

በችግኝ ተከላ መርኃ ግብሩ የዞን የመንግስትና የፀጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎችች በቦታው በመገኘት ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አሳርፈዋል።

መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋና ጉጉት የሚጠብቀው ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን"...
12/06/2026

መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋና ጉጉት የሚጠብቀው ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል -
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

"ኢትዮጵያ እየመከረች ነው"

Address

Asosa
ASSOSA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቡራ ሻንጉል ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አቡራ ሻንጉል ሚዲያ:

Shortcuts

Share