10/10/2017
# FBC የ2010 የቴክኒክና ሙያ መግቢያ መቁረጫ
ነጥብ ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ)
የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ
የ2010 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ መግቢያ መቁረጫ
ነጥብን በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል።
ኤጀንሲው ለጣቢያችን በላከው መግለጫ በ2010
ዓ.ም በሃገሪቱ በሚገኙ 1 ሺህ 357 የቴክኒክና ሙያ
ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ተማሪዎች ተቀብለው
በተለያዩ ደረጃዎች እንደሚያሰለጥኑ ገልጿል።
በዚህ መሰረት በደረጃ 1 እና 2 ለታዳጊ ክልል
ወንዶች አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 2 ነጥብ
29 እና ከዚያ በታች ሲሆን፥ ለሴቶች ደግሞ 2 ነጥብ
14 እና ከዚያ በታች።
ለታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች
ወንዶች 2 ነጥብ 14 እና ከዚያ በታች፥ እንዲሁም
ለሴቶች 2 ነጥብ እና ከዚያ በታች ሆኗል።
ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች ደግሞ 1 ነጥብ 57
እና ከዚያ በታች።
ለደረጃ 3 እና 4 ሰልጣኞች 10ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ፥
ለወንዶች ታዳጊ ክልሎች አርብቶ አደር አካባቢን
ሳይጨምር 2 ነጥብ 43 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም
ለሴቶች 2 ነጥብ 29 እና ከዚያ በላይ ይሆናል።
ለታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች
ወንዶች 2 ነጥብ 29 እና ከዚያ በላይ ሲሆን፥
ለሴቶች ደግሞ 2 ነጥብ 14 ከዚያ በላይ።
ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች ደግሞ 1 ነጥብ 71
እና ከዚያ በላይ።
12ኛ ክፍልን አጠናቀው በደረጃ 3 እና 4 መሰልጠን
ለሚፈልጉ ደግሞ፥ ለወንዶች ታዳጊ ክልሎች አርብቶ
አደር አካባቢን ሳይጨምር 269 እና ከዚያ በታች፥
እንዲሁም ለሴቶች 264 እና ከዚያ በታች።
ለታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች
ወንዶች 249 እንዲሁም ለሴቶች 244 እና ከዚያ
በታች ሆኗል።
ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 169 እና ከዚያ
በታች።
በደረጃ 5 መሰልጠን ለሚፈልጉት ደግሞ የ12ኛ
ክፍል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የወሰዱ
ሆነው፥ ለወንዶች ታዳጊ ክልሎች አርብቶ አደር
አካባቢን ሳይጨምር 270 እና ከዚያ በላይ።
ሴቶች ታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢን
ሳይጨምር 265 እና ከዚያ በላይ ይሆናል።
ለወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር
አካባቢዎች 250 እና ከዚያ በላይ ሲሆን፥ ለሴቶች
ደግሞ 245 እና ከዚያ በላይ።
እንዲሁም ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 170 እና
ከዚያ በላይ ሆኗል።