21/05/2025
"ፋኖ እንደ አንበሳ ክንደ ብርቱ፣ እንደ ነብር ቁጡ፣ እንደ እርግብ የዋህ ነው። በዚህ ባሕርዩም አልጋ ላይ የዋለን በሽተኛ ጠያቂ፣ የተጣላውን አስታራቂ፣ የደከመውን አነቃቂ፣ ለእኔ ሳይሆን ለእኛ የሚል ክንደ ብርቱ የዓላማ ሰው ነው። ፋኖ ቁሞ ከሚሸነፍ ሞቶ ማሸነፍን የሥነ ልቡናው መሠረት ያደረገ የአሸናፊነት ምልክት ነው። ፋኖ የዐማራ ሕዝብ ሥሪት ሕያው ምስክር፣ በራሳቸው የሚተማመኑ ሀገር እና ወገን ወዳድ ስመጥር ጀግና ኢትዮጵያዊያን የክብር ስም ጭምር ነው። ፋኖነት በሕይወት እና በሞት መካከል በሚደረግ ብርቱ ትግል የሚገኝ ወርቃማ ስም ነው። ፋኖነት የዕድሜ፣ የፆታ፣ የሃይማኖት፣ የብሔር፣ የቋንቋ፣ የሙያ፣ የዘር እና መሰል ልዩነቶችን ሳይፈጥርና ሳያጎል ሁሉም በተግባር ተመዝኖ በሚገለጥ እውነታ የሚገኝ እና ራሳቸውን ለሰፊው ሕዝብ ሲሉ አሳልፈው የሚሰጡ ሰዎች ክብር ስም ነው።"