BETA Fashion Design ቤታ ፋሽን ዲዛይን

BETA Fashion Design   ቤታ ፋሽን ዲዛይን Beta Fashion design is a private firm which provides quality Fashion design illustrations and cloth Are you interested in Graphics and Fashion design?

If you say yes this is the right place. You will get updated design and news on the graphics and fashion world. please like and shear the page to appreciate and support our team.

እናት እና ልጅ
14/08/2022

እናት እና ልጅ

 !
30/09/2021

!

Basic Trouser without dart.You can draft it the way I did the basic trouser with dart just that- you have to go in at th...
24/07/2021

Basic Trouser without dart.

You can draft it the way I did the basic trouser with dart just that
- you have to go in at the Centre Front by 1 cm and the difference between the hip and waist to shape the side of the trouser.

 #ለተለያዩ እስፓርታዊ እንቅስቃሴ የሚሆኑ ልብሶችን ለማዘጋጀት የሚያገለግሉ ፓተርኖች!  ዲዛይኖች መገኛ!
22/06/2021

#ለተለያዩ እስፓርታዊ እንቅስቃሴ የሚሆኑ ልብሶችን ለማዘጋጀት የሚያገለግሉ ፓተርኖች!

ዲዛይኖች መገኛ!

  creatives! 's make this outstanding by sharing for our friends  ምድር!
27/05/2021

creatives!
's make this outstanding by sharing for our friends

ምድር!

  ይጨምራል!
27/05/2021

ይጨምራል!

  ምንድን ነው!  ማለት ይቻላል?
19/05/2021

ምንድን ነው!

ማለት ይቻላል?

18/05/2021

ይገርማል፤ይህንን ያውቁ ኖሯል⁉️🤔
#ሰከላ ማን ናት? የኤዶም ምድር....
*እንኳን ወደ የኤዶም ምድር ሰከላ በሠላም መጣችሁ።ሰከላ ጥንታዊ ስሟ ኤዶም ይባላል።በዘፍጥረት ከኤዶም በስተምሥራቅ ገነት ትገኛለች።ገነትን ከሚያጠጡ አራቱ አፍላጋት አንዱ ግዮን ነው።ግዮን ከኤዶም ወይንም ከሰከላ መንጭቶ ኢትዮጵያን 7 ጊዜ ይዞራል።(ዘፍ 2፥1-13)
*አዳም ከአባቱ ከመሬት ተፈጠረ።የተፈጠረበት አፈር "ስውሩ አፈር" ይባላል።የተፈጠረበት ቦታ "ኤልዳ" ትባላለች።ኤልዳ አሁንም ጎጃም ውስጥ አስሌዳውያን ( ኤልዳውያን) የሚባል ቦታ አለ።ኤልዳ ከግዮን በቅርብ ርቀት የምትገኝ ናት።አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ኤልዳ ላይ ከተፈጠረ በኋላ በኤዶም በስተምሥራቅ ወደምትገኘው እንዲሁም የግዮን ወንዝ ወደሚያረሰርሳት ገነት በ40ኛ ቀኑ ፈጣሪው አስገባው።አዳም በገነት የኖረው ለሰባት ዓመት ነው።
*በዘፍጥረት ግዮን (አባይ) ዙሪያ የሚያበራ ዕንቁና የሚያብረቀርቅ ዕንቁም ይገኝበታል።ይኼ ቦታ በጎጃም በስተምዕራብ "ፋዞግሊ" የሚባለው የወርቅ ማውጫ ሳይሆን እንዳልቀረ ሳይንሳዊ ጥናቶች እየወጡ ናቸው።
"ፋዞግሊ" የሚባለው የወርቅ ማውጫ ቦታ ንጉሥ ድግናዣን ለመቆጣጠር 100 ሺህ የሚያህል ሠራዊት ይዞ በበጌምድር በኩል ሲዘምት በአሸዋ ተውጦ ቀርቷል። ዐፄ ካሌብ በአገዎች ያስጠብቀው ነበር።በደቡብ ገናና የነበረው የዳሞት መንግሥትም ይህንን የወርቅ ማውጫና የወርቅ ጎዳና ለመቆጣጠር ወደ ሰሜን ተጉዞ ነበረ።የዛግዌ መሥራች መራ ተክለ ሃይማኖትም በዚህ የወርቅ ጎዳና ጥበቃ ላይ ከተሠማሩት ኃያላን የጦር አዛዦች መካከል አንዱ ነበረ።
*አዳም በሰባተኛ አመቱ ከገነት ከተባረረ በኋላ በአጠቃላይ በምድር ላይ የኖረው 930 ዓመት ነው። የተቀበረው ኮሬብ በሚባል ቦታ ነው።በኢትዮጵያ ኮሬብ የሚባሉ ብዙ ቦታዎች አሉ።በታሪክ የሚታወቀው ግን አምሓራ ሳይንት የሚገኘው ነው።የዮቶር (ካህን ራጉኤል) መኖሪያ እንደነበሩ አሳማኝ ማስረጃዎች እየወጡ ናቸው።ሙሴ በግ የሚጠብቅበት የነበረ ተራራ ተብሎ ይታመናል።
*ግዮን ሰከላ (ኤዶም) ከሚገኘው ግሽ ከተባለው በደን የተሸፈነ ረግረጋማ ቦታ ላይ ይመነጫል።ግሽ ተራራ 2800 ወደ ላይ ይረዝማል።ከተራራው ግርጌ 100 ሜትር ፈንጠር ብሎ አባይ ይወለዳል፡፡ግዮን በሰከላ (በኤዶም) የስያሜ ምንጭም ነው፡፡የአማራ ሕዝብ የበኩር ልጁን "አባይነህ" ይላሉ ታላቅ ነህ ለማለት ነው።
*ግሽ ላይ የጻዲቁ አቡነ ዘርአብሩክ ገዳም ይገኛል።ጻዲቁ አቡነ ዘርአብሩክ በ17ኛው መክዘ ግሽ አባይ ላይ ተቀምጠው ሲጸልዩና ሲያስተምሩ፤ሲያጠምቁበትና ሲፈውሱበት ነበረ። አቡነ ዘርዐ ብሩክ በዚህ ዓይነት የቅድስና ተግባር ቆይተው መጽሐፎቻቸውን በጨርቅ ሸፋፍነው በዓባይ ምንጭ ውስጥ ደብቀዋቸው ወደ ጎንደር ሔዱ።ከሰባት ዓመት በኋላ ወደ ቦታው ተመልሰው መጽሐፎቻቸውን ለማግኘት ከምንጩ አናት ላይ ቆመው፣ለዐራት ጊዜ ጸሎት አድርሰው ከጨረሱ በኋላ “ግሥዒ ግዮንመጻሕፍትየ” (ግዮን ሆይ መጽሐፎቼን ትፊ) ሲሉ መጽሐፎቹ አቧራ እንደለበሱ፤ ርጥበት ሳይኖርባቸው ተንኳፈው ወጥተዋል፡፡ከዚያም ለጓደኛቸው፤ “አባ ይህንን ተአምር እይ” በማለት አሳዩዋቸው፡፡ከዚህ በኋላ የቦታው ስም በግእዝ ግሥዒ ዓባይ ያሉት ቃል ተቀይሮ ግሽ ዓባይ እንደተባለ፤ቦታውም ከገነት ወደ ዓለም እንደ ቧንቧ በሚፈስሰው ጸበል የተባረከና የተቀደሰ፤ ልዩ ምሥጢርም ያለው ውኃ እንደሆነ አባቶች ያስረዳሉ።
*በዚህ ዓይነት የግሽ ዓባይ ጸበል ከውኃው አናት ላይ ሲነሣ እንደ ትንሽ ምንጭ ይሆንና እዚያው ሰከላ (ኤዶም) ትንሽ ወረድ ሲል ደግሞ ማዕበል እየሆነ የግልገል ዓባይን ድልድይ ያቋርጥና በጣና ላይ እየሰፈፈና ቁልቁል ወደ ጢስ ዓባይ እየጎረፈ፤ በደጀን በኩል ወደ ሱዳን ካርቱም፤ ግብጽና ወደ ሜዲትራንያን ባሕር ወርዶ ይቀላቀላል፡፡
*ከዚህ ጋር በተያያዘ፦
1.ኖህ ከማየ አይኅ የጥፋት ውኃ ልጆቹ፣ሚስቱና የልጆቹ ሚስቶች የዳኑት በመርከብ ነው።የኖኅ መርከብ ማየ አይኅ መጉደል ሲጀምር በ7ኛ ወር ከወሩም በ27ኛው ቀን በአራራት ተራሮች ላይ ተቀመጠች።የኖኅ መርከብ ሐመር ያረፈችበት ስሙ ሉባር ተራራ ይባላል።አራራት ተራራ ደግሞ የሚገኘው ከዚሁ ጣና ውስጥ ነው።ኖኅ መርከቧ በአረፈችበት አራራት (ዘጌ) አካባቢ ወይን ሲተክል ኖረ። አካባቢውን ሳይለቅ ከጥፋት ውኃው በኋላ 350 ዓመት ኖረ።በኋላም የተቀመጠው በእንተላ፣በአይዋርካ፣በሽሌ፣በአይከል ቀሪ ዘመኑን የገፋ ሲሆን ጭልጋ ሳለ ሚስቱ እሜቴ አይከል አረፈች።የኖኅ ሚስት እሜቴ አይከል የተቀበረችው ጭልጋ ላይ ነው።በዚህም የጭልጋ ዋና ከተማ በስሟ አይከል ተባለች።ጭልጋ የአራራት ተራራ አዋሳኝ መሆኑ ይታወቃል።
2.ከእሜቴ አይከል እረፍት በኋላ ኖኅ ጎንደር ላይ ብዙ ዘመን ፈጣሪውን እያመሰገነ እየቀደሰ ኖረ።በ950 ዓ.ዓ ኖህ ሲሞት እዛው ጎንደር ላይ ተቀበረ።መቃብሩ ላይ ምንጭ ፈልቆ በርካታ ሰዎችን ይፈውስ ነበር።ከዚያም ለኖህ መታሠቢያ ይሆን ዘንድ አምላክ በቤተመንግስት አሳቦ የኖህ የመቃብር ሐውልት እንዲታነጽ ፈቀደ።ይህም በኋለኛው ዘመን በንጉሥ ፋሲለደስ የታነጸው የፋሲል ግንብ ነው።
3.በሌላው ዓለም በየትኛውም ስፍራ ወይም ምድር በተባለችው ፕላኔት ላይ በየትኛውም አገርና አህጉር የማይገኙ በኖኅ መርከብ ውስጥ ከነበሩት 7ቱ አጥቢ እንስሳት እንደ ዋሊያ፣ቀይ ቀበሮ፣ጭላዳ ዝንጀሮ የመሳሰሉት እና 13ቱ አእዋፋት የሚገኙት ከኢትዮጵያ 1ኛ ከአፍሪካ 4ተኛ ደረጃ ላይ በተቀመጠው የከፍታ መጠኑ 4620 ሜትር በሆነው በራስ ደጀን ተራራ ነው።ደጀን ተራራ በ1970 ዓ.ም.በዩኔስኮ አማካኝነት በአለም የቅርስ መዝገብ ላይ ተመዝግቧል።
4.ሊቀ ነብያት ሙሴን የአመራርነት ጥበብ የተማረው ከአማራ ካህን ዮቶር (ራጉኤል) ነው።ልጁንም ሲጳራ አግብቶ አልአዛር እና ጌርሣም የሚባሉ ልጆችንም ወልደዋል። መሴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ያረፈው በጥንቱ በጌምድር ግዛት ምድያም ነው። ምድያም በዛሬው አማራ ሳይንት ውስጥ መደጊም ተብሎ የሚጠራው ቦታ ነው።
በግ ማርባት በምድያም (በቤጌምድር) ምድር የተለመደ ነው።የአማራ ክፍል የሆነው በጌምድርም የበግ ሀገር የተባለው በግ በማርባት ስለሚታወቅ ነው።በጌምድር ወይንም ሽሜ የአማራ ሀገር ነበር።እስከ ተድባባ ማርያም ድረስ በጌምድር ይባል ነበር።በታሪከ ነገሥት "ወዘዐምሐራ ወዘበጌምድር"ይለዋል።ምድያም የሚባል ቦታ በጂዎግራፊያዊ ማስረጃዎች በሲና ሰርጥ ደቡባዊ ክፍል ይገኛል።ይኼም አካባቢ በሲና ተራራ አጠገብ በመሆኑ ግመል እንጅ በግ ሊያረባ አይችልም።
5.የሌዋዊያን ካህናት ከእስራኤል በመጀመሪያው ፓትርያርክ አዛሪያስ መሪነት የመዝሙረኛው ዳዊት የወንድም ልጅ ሳቤቅ ጨምሮ ወደ ኢትዮጵያ ታቦተ ጽዮንን ተከትለው ከመጡት አስራ ሁለት ሺህ ነገደ እስራል ሁለት ሺህ አመስት መቶዎቹ ተከዜን ተሻግረው ወደ አምሐራ ሳይንት መጡ።ሊቀ ካህን አዛርያስ በጣና ቂርቆስ ሊቀካህን በመሆን መንፈሳ አገልግሎት ሰጥተዋል።ዛሬም ድረስ አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለውና ከአናቱ ላይ እንደ ሙቀጫ የተቦረቦረው ድንጋይ ለዚህ ህያው ማሳያ ነው።የኦሪታውያን የብረት መስዋዕት ማቃጠያም ይገኛል።
6.የጣና ቂርቆስ ገዳም ለሙሴ የተሰጠው የቃል ኪዳን ታቦቱ 800 ዓመት ቆይታበታለች።እንደገና ድንግል ማርያም ልጇን ይዛ ወደ ምድረ ግብጽ በተሰደደችበት ወቅት ለ3 ወራት ከ10 ቀን በዚሁ ገዳም ከልጇ ጋር ቆይተውበታል።ድንግል ማርያም በገዳሙ የነበራትን ቆይታ አጠናቃ ስትመለስ “ፀአና በደመና” በደመና ጫናት የተባለው በጊዜ ብዛት ለአሁኑ የሀይቁ መጠሪያ ስም “ጣና” መሰረት ሆኗል።
7.ቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያውን የዜማ መጽሐፉን የፃፈውና ብዙ ተግባራትን ለመከወን የመረጠው ጣና ቂርቆስን ነው፡፡መጽሐፍ ሲጽፍ ለጥቁርና ቀይ ቀለማት መበጥበጫነት ይጠቀምባቸው የነበሩ ከድንጋይ ተቦርቡረው የተሠሩ ጉድጓዶች፣የቅዱስ ያሬድ ድጓና ካባ በገዳሙ ይገኛሉ።
8.ግማደ መስቀሉ የሚገኘው ቤተ-አምሓራ ግሼ ነው።መስቀሉን ከግብፅ በሰሜን ጎንደር በስናር በኩል ወደ ተጉለት (ሸዋ) ያስመጡት የበረራን ወይንም የአዲስአበባን ከተማ የቆረቋሯት ቀዳማዊ ዐፄ ዳዊት ናቸው።መስቀሉን በመስቀለኛ ቦታ በግሼ ተራራ ያስቀመጠው ደግሞ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ነው።
9. ቅዱስ ኡራኤል የጌታን ደም የረጨበት የሚገኘው ሰሜን ሸዋ መንዝ ነው።ቅዱስ ኡራኤል የክርስቶስን ደም የረጨበትን ጽዋ የሰወረው መንዝ እመጓ ቆጵሮስ ተራራ ላይ ነው።የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰይፍ የተሰወረው፣
ቅዱስ ጊዮርጊስ ያረፈው፣የቅዱስ ጊዮርጊስ የፈረሱ አሻራ ኮቲ የሚገኘው ከዚሁ ቆጵሮስ ተራራ ነው።
*በዚህ መረጃ አግባብ
1.ኤዶም
2.ግዮን
3.አዳም
4.ኖኅ
5.አራራት ተራራ
6.ጣና
7.ጣና ቂርቆስ
8.እሜቴ አይከል ጭልጋ)
9.ፋሲለደስ (የኖኅ መቃብር)
10.ግሼን (ግማደ መስቀሉ
11.ቤተ አምሓራ (ሳይንት)
12.መንዝ (እመጓ ቆላ) እና ሌሎችም ቅዱስ ቦታዎች በሚገባ ሊጠኑ ይገባል።
በርግጠኝነት የዓለም ታሪክ ይገለበጣል።የዓለም አይኖች ሁሉ ወደ ግዮን ምንጭ ይሆናል።ምንጭ:-{Getu Addis}

18/03/2021
01/03/2021

የእቴጌ ጣይቱ የአድዋ ገድል የሚጀምረው ለአድዋ ጦርነት መነሻ ከሆነው ከውጫሌ ስምምነት ነው፡፡ ኮንት አንቶኔሊ የውጫሌ ውል እርሱ እንደፈለገው እንደማይሆን እና 17ኛዋ አንቀፅ እንደተሰረዘ በሰማ ጊዜ እቴጌ ጣይቱ እና አጤ ምኒልክ በተቀመጡበት እልፍኝ ገብቶ "የ 17ተኛዉ ክፍል ተሰርዞአል ተብሎ ተፃፈ" በማለት አጤ ሚኒልክን ይጠይቃል።አጤ ሚኒልክም "ሁለታችን አንተና እኔ ተነጋግረን አንተ ወደህና ፈቅደህ የተፃፈ ቃል ነዉ ሌላ አልታከለበትም ባስተርጐሚህ የተናገርከዉ ነው" አሉት።

ከዛ ኮንት አንቶኔሊ እንዳልተሳካለት አውቆ የውሉን ወረቀት በጫጨቀውና ጦርነቱ እንደማይቀር ተናግሮ ከእልፍኝ እየወጣ እያለ እቴጌ ጣይቱ ከት ብለዉ በመሳቅ

" የዛሬ ሳምንት አድርገው በዚህ የሚደነግጥ የለም። ሂድ የፎከርክበትን አድርግ እኛም የመጣውን እናነሳዋለን። እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር ሰጥቶ አገሩን የማያድን ሰው ከዚህ የሌለ አይምሰልህ የገዛ ደሙን ገብሮ ለገዛ አገሩ መሞት ጌጥ ነው እንጅ ሞት አይደለም አሁንም ሂድ አይምሽብህ የፎከርክበትን በፈቀደህ ጊዜ አድርገው እኛም ከዚሁ እንቆይሀለን፤

“ያንተ ፍላጐት ኢትዮጵያ በሌላ መንግስት ፊት የኢጣሊያ ጥገኛ መሆኗን ለማሳወቅ ነው። ነገር ግን ይህን የመሰለው የምኞት ሃሳብ አይሞከርም!! እኔ ራሴ ሴት ነኝ። ጦርነት አልፈልግም። ነገር ግን ይህን ውል ብሎ ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ!” በማለት ፈፅሞ በኢትዮጵያ ሉአላዊነት እንደማይደራደሩ መናገራቸውን ጳውሎስ ኞኞ አጤ ምኒልክ በሚለው መፅሃፍ አስፍረዋል፡፡

እቴጌ ጣይቱ ሴቶችን በማስተባበር ትልቅ ስራም ሰርተዋል፡፡ እቴጌ ጣይቱ በአድዋ ዘመቻ ወቅትም የራሳቸውን ጦር እየመሩ ዘምተዋል፡፡

ጣሊያኖች ወደ መቀሌው ምሽግ በተሸሸጉ ጊዜም ይህን ሁኔታ የተገነዘቡት እቴጌይቱ የጣሊያኖችን የውኃ ምንጭ በራሳቸዉ ጦር በማስከበብ እና ምንጩን በማሳገድ ውሃ ሲጠማቸው ሽንፈታቸውን እንዲቀበሉ አድርገዋል፡፡ ይህ በመቀሌ የሚገኘው ምንጭም እስከዛሬ ድረስ ውሃ የሚያፈልቅ ሲሆን ለንግስቲቱ መታሰቢያነት ይሆን ዘንድ
‹‹ ማይ እንስቲ›› ተብሎ ተሰይሟል፡፡ትርጓሜውም የሴት ውሃ ማለት ነው፡፡


http://nakyhotel.com/

  በዓል ይሁንልን።
06/01/2021

በዓል ይሁንልን።

 #መልካም የመዉሊድ በዓል
29/10/2020

#መልካም የመዉሊድ በዓል

Address

Addis Ababa

Telephone

+251953902828

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when BETA Fashion Design ቤታ ፋሽን ዲዛይን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share