07/04/2025
አቶ ጌታቸው ረዳ ምስጋና ቀርቦላቸው ከጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንትነት ተሰናበቱ።
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት ሁለት ዓመታት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር በመሆን ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት ሁለት ዓመታት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር በመሆን ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡
በተለይ አቶ ጌታቸው የተገኘው ሰላም እንዲጸና ለነበራቸው ከፍተኛ ጥንቃቄና አመራር የፌደራል መንግስት እውቅና እንደሚሰጥ አስገንዝበዋል፡፡
በቀጣይ ሥራዎች በጋራ ተቀራርበው እንደሚሰሩ ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለነበራቸው ቆይታም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር በመሆን ለሁለት ዓመት መርተዋል። አሁን ላይ አዲስ የክልሉ ፕሬዝዳንት እንዲሰየም ሂደት ላይ ነው።
Fanos midea ፋኖስ ሚድያ