13/01/2026
በሀምበርቾ ተራራ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉ ተገለፀ ።
እሳቱ በተራራው ላይ ባለው ደን ምክንያቱ ባልተወቀ መንገድ የተለኮሰ ሲሆን እሳቱ እንዳይስፋፋ በተራራው የሚዋሰኑ ቀበሌያት፣ ፀጥታ ኃይልና የአካባቢው ማህበረሰብ በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው ብርቱ ጥራት የእሳት አደጋውን መቆጣጠር መቻሉም ነው የተገለፁ።
የዞኑ አስተዳደር እሳቱ የከፋ አደጋ ሳያደርስ ለመቆጣጠር የአካባቢው ኅብረተሰቡ ከመንግስትና ከፀጥታ አካላት ጋር በማበር ባደረገው ከፍተኛ ጥራት የእሳት አደጋው ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የእሳት አደጋው ሙሉ በሙሉ ቁጥጥር ስር እንዲውል ያለሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ሁሉ የዞኑ አስተዳደር ምስጋናውን ያቀርባል።