19/09/2021
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም የደ/ጎንደር ዞን ጽ/ቤት
መኪና ጎማ 7.50 በ16 ባለ12 ክር አዲስ ጎማ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የቀረበውን መስፈርት የሚያሟላ ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራችሁ ነጋዴዎች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ የጨረታው መመሪያበጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ማሟላት ያለባችሁ መስፈርት፡-የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፤የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት ያላቸው፤የግብር ከፋዮች (ቲን) መክፈያ ሰርትፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፤በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎችን ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡ተጫራቾች ለሚሳተፉባቸው አይነት ነጠላ ዋጋና ጠቅላላ ዋጋ በዋጋ መሙያ መሙላት ይገባቸዋል፡፡ በነጠላ ዋጋና በድምር ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው የሚያዝ ይሆናል፡፡ ዋጋ ሲሞላ ስርዝ ካለ ፊርማ ሊኖረው ይገባል፡፡ ሆኖም ግን ስርዝ ድልዝ ከበዛበትና ግልጽነት ከጎደለው ተወዳዳሪው ከጨረታው ይሰረዛል፡፡ ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል የአጠቃላይ የተሞላው ዋጋውን 2 በመቶ ሲፒኦ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ 60 የቀን በአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ደ/ጎንደር ዞን ጽ/ቤት ትክክለኛ ስም በማሰራት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ጨረታውን በወቅቱ አጠናቆ ያላቀረበ ማንኛውም ማስረጃ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ 7ኛው ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል አብቁተ ደ/ጎንደር ዞን ጽ/ቤት ህንጻ 4ኛ ፎቅ ዋና ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 402 ዘወትር በስራ ሰዓት 2፡30 እስከ 11፡30 ድረስ መግዛት ይችላሉ፡፡የጨረታውን ሰነድ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 7ኛው ደ/ታቦር ከሚገኘው አብቁተ ደ/ጎንደር ዞን ፋሲሊቲ ቢሮ ቁጥር 101 አንደኛ ፎቅ ከቀኑ 6፡00 ድረስ ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ኢንቨሎፕ በማሸግ የተወዳደሩበትን ጨረታ አይነት የድርጅቱን ስምና አድራሻ በመጻፍ ማስገባት ይጠበቅባችኋል፡፡ ጨረታው በዚህ እለት ከቀኑ 8፡00 ተጫራቾቹ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በግልጽ ይከፈታል፡፡ ማስረከቢያ ደ/ጎንደር ዞን ደ/ታቦር ከሚገኘው ንብረት ክፍል የሚገዙ መኪና ጎማ 7.50በ16 ባለ12 ክር አዲስ ጎማ አይነት ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 101 የጨረታ ሰነድ ማግኘት ማየት ይቻላል፡፡ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ አማራ ብድርና ቁጠባ ደ/ጎንደር ዞን ቀበሌ 01 ደ/ታቦር ስ.ቁ 0584410659 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡