Extends with me

Extends with me mekelle institute of technologies

10/11/2019

ሴትየዋ ችግሯን ልታማክር ወደ ዶክተር ሄደች።
"ዶክተር እባክህ አንድ ችግር ገጥሞኛል።"
"ምን ገጠመሽ?"
".…ከወለድኩ ገና አንድ አመት አልሞላኝም። ሆኖም ሌላ ልጅ አርግዣለሁ። እኔ ደግሞ ተጨማሪ ልጅ በዚህ ወቅት እንዲኖረኝ አልፈልግም።"
"እና ምን ልርዳሽ?""
"ሆዴ ውስጥ ያለውን ልጅ ማስወረድ እፈልጋለሁ!"
ዶክተሩ ትንሽ አሰብ አደረገና “ለምን ከዚህ የተሻለ ሀሳብ አላቀርብልሽም?” ሲል ጠየቃት።
“ምን አይነት ሀሳብ?”
“አየሽ ይሄን ልጅ ከሆድሽ ለማስወረድ ብዙ ችግር ውስጥ ትገቢያለሽ፣ ደም ይፈስሻል ልትሞቺ ወይም በቀጣይ ላትወልጂ የምትችይበት አጋጣሚም ሊፈጠር ይችላል። ስለዚህ ይሄን ሁሉ ችግር ከምታይ ለምን በእጅሽ ያቀፍሽውን ልጅ አንገድለውም?” አላት
ሴትየው አደነገጠች። ዶክተሩ ንግግግሩን ቀጠለ።
“አዎ! ለእናት እንደሆነ ሁሉም ልጅ እኩል ነው። ስለዚህ አንዱ መሞት ካለበት ሆድሽ ውስጥ ያለው ከሚሞት ይሄኛው የተወለደው ቢሞት ምንም ችግር ሳይገጥምሽ ሀሳብሽን ታሳኪያለች…” እያለ ምክረ ሀሳቡን መተንተን ጀመረ።
ሴትየዋ ግን በጆሮዋ የሚንቆረቆረው የዶክተሩ ሀሳብ ሳይሆን የአምላክ ማሳሰቢያ መሆኑን እያሰበች ለማስወርድ የዘረጋቻቸውን ሁለት እግሮቿን ሰብስባ ብድግ ብላ ክፍሉን ለቃ መውጣት ጀመረች።..…ልጆቿን አንዱን በክንዷ ሌላውን በሆዷ እንዳቀፈች ወደ ቤቷ ተመለሰች። አዎ! የተወለደም በሆድ ውስጥ ያለም ቢሆን ለእናት ልጆቿ ሁሉ እኩል ናቸው!

(ፋሲል በቀለ እንግሊዝኛውን ለጥፎ አገኘሁት እኔ ተረጎምኩት)

ህጻናትን በውርጃ መግደል ወንጀልም ሀጢያትም ነው!

Address

Mekelle
Adi Tigre
LILPACK

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Extends with me posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Extends with me:

Share