Amba 27

Amba 27 discussing and Teaching learning

28/03/2026

ያማል።

23/07/2025

በሁለት ጆሮዋ የምትሰማ ብቸኛ ፍጥረት ማን ናት?

የትንሣኤ ዋዜማ እርድ  ስንት ሰዓት መታረድ እንዳለበት በሰጡት ማብራሪያ ግራ ተጋባን ላሉት ኦርቶዶክሳውያክቡር ሊቀሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ  ያስተላለፉት መልእክት። 👉🏻“መብል ግን ወደ እ...
20/04/2025

የትንሣኤ ዋዜማ እርድ ስንት ሰዓት መታረድ እንዳለበት በሰጡት ማብራሪያ ግራ ተጋባን ላሉት ኦርቶዶክሳውያ
ክቡር ሊቀሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ ያስተላለፉት መልእክት።
👉🏻“መብል ግን ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጎድለንም፤ ብንበላም ምንም አይተርፈንም ዳሩ ግን ይህ መብታችሁ ለደካሞች እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ተጠንቀቁ” 1ቆሮ. 8፥8 የመብልና የመጠጥ ጉዳይ በቤተ ክርስቲያን ከርክር ሁኖ ሊነሣ የሚገባው ዋና አጀንዳ አይደለም። ነገር ግን አይነሣ ነገር የለምና ከተነሣ ፍርዱ የሚሰጠው ምዕመናን እንዳይቸገሩ በሕገ ርኅራሄ የሚዳኝ ነው እንጅ እንደ ሌሎቹ ሃይማኖታዊ ክርክሮች ተጠየቅ ልጠይቅህ የሚል ሥርዓት የሚታይበት አይደለም። ጉዳዩ ሕዝብ እንዳይከፋፍል ተብሎ ካልሆነ ምድራዊ ሥርዓት ስለሆነ ነው። የእግዚአብሔር ሕግ ወንጌል ከሰማይ ስለወረደ እንጀራ የምንማርባት እንጅ ስለምድራዊ መብልና መጠጥ እያነሣን የምንከራከርባት መጽሐፍ ስላልሆነች ነው። ይህንንስ እግዚአብሔር አሳልፎታል፤ በሰማያዊ መና ተክቶታል።
በሰሞኑ ከፋሲካ በዓል እርድ ጋር ተያይዞ የተነሣው ትምህርት የተለያዩ መምህራን ሲይዙት የተለያየ መልስ እየተሰጠበት በመሆኑ ግራ የተጋባችሁ፣ ያዘናችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ ከደረሱኝ መልዕክቶች ለመረዳት ችያለሁ። ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው ሰዎችም ደስታቸውን ገልጸውልኛል። ዛሬ ይህንን መልዕክት ለመጻፍ የተነሣሁትም ለዚህ ነው። አስቀድሜ መግለጽ እምፈልገው በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር ሙግት እንደሌለኝ ነው። ከኔ ጋር የተስማሙትንም ሆነ ያልተስማሙትን ለመንቀፍም ለማመስገንም አይደለም።
እኔ ይህንን መልዕክት ሳስተላልፍ የተናገርሁበትን መንፈስ Intention ላስረዳችሁ። እኔ የተላክሁት ወንጌል እንድሰብክና ምዕመናንን ሁሉ ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም እንዳቀርብ ነው። ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዲወርሱ ከማድረግ በቀር ሌላ ዓላማ የለኝም። የሁሉም የቤተ ክርስቲያን መምህራን ተልዕኮም ይሄ ነው። የአንዲት ቤተ ክርስቲያን መምህራን እስከሆንን ድረስ በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩነት ይኖርብናል ብየ አላምንም። ልዩነት የሚፈጠረው ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ጠርታ በምታገባው በወንጌል ትምህርታችን ሳይሆን በዚህ መካከል ዕንቅፋት የሚሆንባቸውን ነገር እያስወገዱ በመሄድ ጉዳይ ላይ ነው። የዛሬው አከራካሪ ጉዳይም ዕንቅፋትን የማስወገድ ጉዳይ ነው እንጅ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የሚያገባ መሠረታዊ የወንጌል ትምህርት የሚባል አይደለም።
እግዚአብሔር ፈቅዶ ከቀደመው ዘመን ይልቅ ይሄኛው ትውልድ ወደ ቅዱስ ቊርባን የሚቀርብ ትውልድ እየሆነልን ነው። ከአንድ ሰዓት ለሚበልጥ ጊዜ ካህናቱ ቆመው ሲያቆርቡ ስመለከት ነፍሴን ከዚህ በላይ የሚያስደስታት ነገር እንደሌለ ነው ምነግራችሁ። ነገር ግን የፋሲካ ዕለት ለመቊረብ ብዙ ሰዎች ሲቸገሩ ስላየሁ ነው በቪዲዮ ያያችሁትን ትምህርት የሰጠሁት። ከሥጋው ከደሙ የሚከለክለን ምንም አይነት ዕንቅፋት ሊኖርብን አይገባም። በዚያውም ላይ በጾም ደም ማፍሰስ ጾም ያስገድፋል ብሎ ማስተማርም ሃይማኖታችንን ግብዝ ያደርግብናል ሥጋ ባየን ቁጥር ጾም የምንሽር ከሆነ እንዴት ያለ ሃይማኖት ነው አያሰኝብንም? ሥጋ አትብሉ ነው እንጅ አትረዱ የሚልስ ሕግ አለ? ላንበላው ለምን እናርደዋለን? ካላልን በቀር። ደግሞስ ምዕመናን አማናዊውን ፋሲካቸውን ክርስቶስን በልተው ጠጥተው ደስታቸው ፍጹም እንዲሆንላቸው ልናበረታታቸው ሲገባ ማሰናከል አይሆንብንም? ቅዱሳን ሐዋርያት እንዳስተማሩን “ሕዝቡን እንዳናስቸግራቸው” ሥራ. 15፥19 አድርገን ማስተማር ይገባናል። ወጥተው ይረዱት እንዳንል ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ ሊያከናውኑት የሚችሉት ነገር አይደለም፤ ይቅርባቸው እንዳንል በተዐቅቦ የሚኖር መነኩሴ ሳይቀር ሥጋ በልቶ ወይን ጠጥቶ ምስጋና በሚያቀርብበት ዕለት እንዴት ሥጋ ከመብላት እንከለክላቸዋለን? በዓመት ሁለት ጊዜ የልደትና የትንሣኤ በዋልድባና በማኅበረ ሥላሴ በሌሎችም ገዳማት በጽኑዕ ተጋድሎ የሚኖሩ መነኮሳትም ይህንን ቀን ሥጋ ይበላሉ ወይን ይቀምሳሉ። በምዕመናን ላይ እኛ የማንችለውን ቀንበር እየጫንን እንደሆነ ይሰማኛል።
አስቀድመን ወደ ቅዱስ ቊርባን ለመቅረብ የሚከለክላቸው ነገር እንዳይኖር እንጠንቀቅላቸው፤ ምዕመናንም ግራ አትጋቡ አትጨነቁ፤ መዳናችሁን ለመጠበቅ ይሕንን ምክንያት በማድረግ ከሥጋው ከደሙ እንዳትርቁ በቤተ ክርስቲያን ገብታችሁ “ትንሣኤከ ለዕለ አመነ ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ” ብላችሁ መዘመር እንዳይቀርባችሁ አጠናቃችሁ እንድትሄዱ ለማድረግ ነው። ከኔ የተለየ ሀሳብ ያላቸውም ሥርዐተ ጾም እንዳይሻር ብለው ነው። እንዲህ ያለ ነገር ሲያጋጥማችሁ ለወደፊቱም መምህራችን ቅዱስ ጳውሎስ “ለደካሞች እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ተጠንቀቁ” እንዳለ እንደ ድካማችሁ አይታችሁ ዕንቅፋት የማይሆንባችሁን ትምህርት ምረጡ እንጅ ሁለቱም የተለያየ ሆኖባችሁ መሰቃየት የለባችሁም። ሥርዐት ለመሸርሸር ታስቦም አይደለም፤ ከሆነም ከመቊረብ የሚበልጥም የሚቀድምም ሥርዓት የለንም። ከዚህ የሚያርቀን ከሆነ ማንኛውንም ሥርዐት ማስተካከያ ልናደርግበት እንችላለን። በሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ተሹመን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን አናፈርስም።
አእምሯችሁን በሚያሳርፍ የእግዚአብሔር ሰላም ውስጥ ሆናችሁ የምታሳልፉትን የትንሣኤ በዓል በምንም ሁኔታ ልትረበሹ አይገባም የሚል ሀሳብ ስለተሰማኝ ይህንን መልዕክት ጻፍሁላችሁ።
ስምዐኮነ መላክ
ቪድዮውን ላልሰማችሁ ሊንኩን ተጭናችሁ አድምጡ

https://youtube.com/?si=kV_FJW4TX-8qZE3G

15/02/2025

የትግስት ፍሬዋ

06/11/2024

ለአዲሶቹ ተከታዮቼ ምስጋና! በመቀላቀልዎ ደስ ብሎኛል! ሠይድ ሀጂ እብራሁ, Mubarak Abderahaman

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Missale Sch, Yimam Arage, Albakir Asedik, Yihayis Teamno ...
25/09/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Missale Sch, Yimam Arage, Albakir Asedik, Yihayis Teamno Yirga

22/09/2024

ላለመሳቅ ይሞክሩ

22/09/2024

#ዘና

24/06/2024

† ግልጽ ደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ †† ታላላቅ በዓላትን አናደብዝዛቸው።†★ በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን ተብሎ መሰየሙ ትክክል አይደለም። ፕሮቴስታንቱ በፓርላማ በዓለ ሃምሳ ...
22/06/2024

† ግልጽ ደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ †

† ታላላቅ በዓላትን አናደብዝዛቸው።†

★ በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን ተብሎ መሰየሙ ትክክል አይደለም። ፕሮቴስታንቱ በፓርላማ በዓለ ሃምሳ ብለን እንድናከብር ካላንደር ይዘጋጅልን የሚሉት ይህንን ታላቅ ቀን በገዛ እጃችን እያደበዘዝን ነው።★

† በዓለ ሃምሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከትንሣኤ በኋላ በሃምሳኛው ቀን የሚከበር ብሔራዊና ሃይማኖታዊ በዓላችን ነው።†

መጽሐፍ ቅዱስ ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ይላል።1ቆሮ 14፥40 ቀደምት ኦርቶዶክሳውያን አባቶች እያንዳንዷን ዕለት ሲሰይሙና ሥርዐት ሲደነግጉ በብዙ ጥንቃቄና ማስተዋል ተመልተው ነው። በዓላትን ሲሰይሙ በዕለቱ ሊታሰብ ስለሚገባው የቀኑ ባለቤት ሰፊና ጥልቅ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው ይትባሃል ደንግገው ነው።በእያንዳንዷ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች በሙሉ የቀኑን ባለቤት የሚያዘክሩ ናቸው።በማኅሌት፣በሰዓታትና በቅዳሴ፣በስብከተ ወንጌልና በዝማሬ የሚተላለፈው መንፈሳዊ መልዕክት ሁሉ ዕለቱን መሠረት ያደረገ ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ያለው ግዴለሽነትና በቀደሙ አባቶች መንገድ አለመሄድ የቤተክርስቲያኒቱን ክብር በማይመጥን መንግድ ከሥርዓት የወጡ እንግዳ ድርጊቶች ሲፈጸሙ እየተመለከትን ነው።

ሁላችን እንደምናውቀው ጰራቅሊጦስ ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል የሆነው መንፈስ ቅዱስ ነው።መንፈስ ቅዱስ ደግሞ የቤተክርስቲያን ሕይወት ነው።እያንዳንዱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንና ልዩ ልዩ አገልግሎቶች ሁሉ የሚከናወኑት በመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ኃይል ነው።ያለ መንፈስቅዱስ እገዛ ቤተክርስቲያን የምታከናውነው አንዳችም ዓይነት አገልግሎት የለም።ይሁን እንጂ ለመንፈስ ቅዱስ የሰጠነው ቦታና ክብር ልንሰጠው የሚገባውን ያህል መንፈሳዊ ደረጃውን የጠበቀ አይደለም።

ለምሳሌ ያህል እግዚአብሔር አብ ብለን የሰየምናቸው በርካታ አብያተ ክርስቲያናት በመላ ሀገሪቱ ሞልተዋል፣በእግዚአብሔር ወልድ ስም የተሰየሙ አብያተ ክርስቲያናትም እጅግ በርካቶች ናቸው፤ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተሰየመ የጰራቅሊጦስ ቤተክርስቲያን ግን ፈልጎ ማግኘት እጅግ ከባድ ነው።መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር በሥልጣን በአገዛዝና በመለኮት አንድ የሆነ የራሱ የሆነ ፍጹም መልክ፣ፍጹም ገጽ ፣ፍጹም አካል ያለው እግዚአብሔር ነው ብለን በምሥጢረ ሥላሴ አስተምህሯችን እስካስተማርን ድረስ ለመንፈስ ቅዱስ ልንሰጠው የሚገባው ክብርና ቦታ ከአብና ከወልድ ያልተናነሰ እኩል የሆነ አገልግሎት ሊሆን ይገባል።አሊያ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ያንሳል የሚለውን የመቅዶኒዮስን ስሑት ሐሳብ በቃል እየተቃወምን በተግባር ግን እየተከተልን ነው።

እንዲህ ለማለት የተነሳሁበት ምክንያት በአዲስ አበባ ጎላ ሚካኤል ተብሎ የሚጠራው ቤተክርስቲያን ሲመሠረት የጰራቅሊጦስ ቤተክርስቲያን ነበር፤ ነገር ግን ስለመንፈስ ቅዱስ ክብር፣በመንፈስ ቅዱስ ስለሚገኘው ኃይልና ጸጋ ፣ስለ መንፈስ ቅዱስ ልዩ መለኮታዊ አሰራር በሚገባ ሕዝቡን ስላላስተማርን ወደዛ ቤተክርስቲያን የሚሄደው ሕዝብ ጥቂት ስለሆነባቸው ካህናቱ የሚካኤልን ታቦት አስገብተው ሕዝቡን ሚካኤል መጥቶላችኋል እያሉ ስለሰበኩት እጅግ በርካታ ሕዝብ መሄድ ጀመረ በዚህም የተነሳ ጎላ ሚካኤል ተባለ።ከመንፈስ ቅዱስ ይልቅ ሚካኤል ጎልቶ እንዲታይ ያደረገ ትምህርትና ሥርዓት ሕዝቡን በማስለመዳችን እስከዛሬ ድረስ ጎላ ሚካኤል ሲባል ይጠራል።ደብሩ ተሰይሞበት የነበረው ጰራቅሊጦስ ግን በዓመት አንዴ እንዲታሰብ ቢደረግም እስከዛሬ የሚካኤልን ያህል ክብርና ቦታ አላገኘም።

ወገኖቼ በጣም እናስተውል ቅዱሳን መላዕክትን ማክበር በጣም ተገቢ ነው።ምልጃና ጸሎታቸው እንዲያግዘን መማጸንና ጥበቃቸው እንዳይለየን መትጋት ሁላችን ልንጠብቀው የሚገባ ኦርቶዶክሳዊ ሥርዓታችን ነው፤ ነገር ግን አምላክ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ከመልአክ በታች አሳንሰን ተገቢውን ሥፍራ አለመስጠት ፍጹም ስህተት ነው። ይህ ሁሉ የትምህርት እጥረትና ከእግዚአብሔር ክብር ይልቅ ገንዘብ የሚያስገኝልን የትኛው ነው በሚል ሥጋዊ አስተሳሰብ የሚመጣ ኢኦርቶዶክሳዊ አካሄድ ስለሆነ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስና ጠቅላይ ቤተክህነት እንዲህ ዓይነት ነገሮችን አጥብቆ ሊያስተካክል ይገባል።

እጅግ የሚያሳዝነው የቤተክህነቱ ቸልተኝነትና ግዴለሽነት በዚህ ሳያበቃ በዓመት አንዴ የሚታሰበውን በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሚል ሌላ ግርዶሽ መከለሉ እጅግ ያሳፍራል።ቀደምት አባቶች በዓለ ጰራቅሊጦስን እንድናስብ ሥርዓት ሲሰሩልን በዕለቱ ስለመንፈስ ቅዱስ አሰራር፣ስለ መንፈስ ቅዱስ ኃይልና ሥልጣን ፣ስለመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በሰፊው ትምህርቶች እንዲሰጡ፣ለመንፈስ ቅዱስ ዝማሬና ቅኔ ከወትሮ በተለየ እየቀረበ ዕለቱን እንድናስብ ነበር።አሁን ግን ይህ ሁሉ እንዲድበሰበስና እንዲኮስስ የሚያደርግ ሥርዐት እየተሰራ መሆኑን እያየን በመሆኑ በፍጥነት ሊስተካከል ይገባል።ምክንያቱም በጊዜ ሂደት ልክ እንደ ጎላ ሚካኤል መንፈስ ቅዱስ እየተረሳ ይሄድና የሰንበት ትምህርትቤቶች ሪፓርትና የሥራ ዕቅድ የሚቀርብበት የስብሰባ ቀን ሆኖ ይቀራል።

አንባብያን እዚህ ላይ በጣም አስተውሉ የሰንበት ትምህርትቤቶች ቀን ማሰብ ተገቢነው።ነገር ግን ቀኑ በመንፈስ ቅዱስ በዓል ላይ መደረብ የለበትም።የሰንበት ትምህርትቤቶች ቀን እኮ ትልቅ ቀን ነው።በዕለቱ ስለ ሰንበት ትምህርት ቤት ጥቅም፣በሰንበት ትምህርት ቤት ስላለፋ አባቶችና መምህራን የሥራ ፍሬ በስፋት የሚዘከርበት እንዲሁም ወጣቶች ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሰፊ ቅስቀሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት የሚተላለፍበት ቀን ነው።ታዲያ ሁለት ታላላቅ በዓላትን አንድላይ ማደራረብ ፍጹም ስህተት ነው።

ፕሮቴስታንቱ ፓርላማ ውስጥ ለመንግሥት እያቀረቡ ያለውን ጥያቄ ሁላችን ተከታትለናል።በዓለ ሃምሳ የሚባል ቀን በካላንደር የሚዘጋ ዕለት ያስፈልገናል ብለው እየተሟገቱ ነው።ይህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ክብርና ሉዓላዊነት የሚገፋ ጥያቄ ነው።ምክንያቱም በዓለ ሃምሳ ከትንሣኤ በኋላ በሃምሳኛው ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዐት የሚከበር ብሔራዊ ሃይማኖታዊ በዓላችን ነው።ስለዚህ ሉዓላዊ ክብራችንን ማስደፈር የለብንም።

ሁላችን እንደምናውቀው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ወር በገባ በስድስት ኢየሱስ ተብሎ እንዳይጠራ ተደርጎ በአርሴማ በመተካቱ አዲሱ ትውልድ ኢየሱስን ሳይሆን አርሴማን በዕለቱ እያከበረ እንዲውል ተደርጓል።ቀደምት ኦርቶዶክሳውያን አባቶች ግን ይህንን ዕለት ኢየሱስ ብለው ሲሰይሙ በምክንያት ነው።በዕለቱ ከሌሎች ቀናት በተለየ ሁኔታ የኢየሱስን ክብር፣ የኢየሱስን አዳኝነት፣ከኢየሱስ ጋር በመሆን የሚገኘውን ጽቅና በረከት በሰፊው እንዲሰበክበት፣ስለ ኢየሱስ በሰፊው እንዲዘመርበት ነበር ፤ አለመታደል ሆኖ ግን የእነዚህ ዓይናማ ሊቃውንት ሥርዓት ተጥሶ እየተፈጸመ ያለው አዲስና እንግዳ ልማድ ሕዝቡ ኢየሱስን ከራሱ ቤት ይልቅ በሌሎች ድንኳን እንዲፈልገው እየገፋው ይገኛል።አንድ ጅል የተከለውን ሰባት ብልህ አይነቅለውም የሚባለው እንደዚህ ዓይነቱ ነውና ቅዱስ ሲኖዶስና ጠቅላይ ቤተክህነት በዚህ ጉዳይ በጥልቀት ሊያስቡበትና ሊያስተካክሉት ይገባል ግዴለሽነት የምንደኛ እረኛ ጠባይ ነው።

አሁን አሁንማ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ በገንዘብ ፍቅር ዓይናቸው የታወረ ካህናት ኢየሱስን በዕለቱ ከማሰብና በስሙ መቅደሱን ከመትከል ይልቅ ሕዝብ ሊስብልን የሚችለው የትኛው ነው በሚል ሥጋዊ አስተሳሰብ ላይ ብቻ ሲራኮቱ እያየን ነው።በዚህ ድርጊታችሁ ትውልዱን ወደ ሌላ ቤተእምነት ትገፋታላችሁ እንጂ ሌላውን ወደ ኦርቶዶክስ ማምጣት ፈጽሞ አትችሉምና ከገንዘብ ይልቅ ትውልዱን በክርስቶስ ፍቅር ነፍሱን እንዴት ማዳን እንደምትችሉ አትኩራችሁ ሰፊ ሥራ ሥሩ።

" ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ።" 1ቆሮ14፥40

መ/ር ታሪኩ አበራ

ለሌሎችም ሼር አድርጉት

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amba 27 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share