04/02/2026
ብራዚላውያን ጥንዶች ለ20 ዓመታት ያክል በትዳር ከኖሩ በኋላ የአንድ እናት ልጆች መሆናቸውን ማረዳታቸው አነጋጋሪ ሆኗል።
አድሪያና እና ሊዮናርዶ የተባሉት ጥንዶች ከእናታቸው ጋር በልጅታው የተለያዩ ሲሆን እናቸው ማን እንደሆነች አያውቁም ነበረ።
ጥንዶቹ የአናታቸው ስም ማሪያ እንደመባል ቢያውቁም ጉዳዩን የስም መመሳሰል እንደሆነ አድርገው ቆጥረውት ነበረ። አድሪያና እና ሊዮናርዶ ወላጅ እናታቸውን ለማፈላግ ወደ አንድ ሬዲዮ ጣቢያ ጎራ ካሉ በኋላ ነው ያልጠበቁት ነገር የተከሰተው።
ጥንዶቹ የተጠፋፉ ቤተሰቦችን በሚያገናኝ ሬዲዮ ጣቢያ ላይ እናታቸውን ለመፈለግ ያመለከቱ ሲሆን ከቆይታ በኋላ ያገኙት ምላሽ ግን አስደንጋጭ ሆነው አግኝተውታል። ጥንዶቹ ለ20 ዓመታት በየፊናቸው ሲፈልጓት የነበረችው እናታቸው አንድ ሰው ሆና ተገኝታለች።
አድሪያና እና ሊዮናርዶ ከተለያየ አባት በመወለዳቸው እና ከእናቸው ጋር በልጅነታቸው በመለያየታቸው ነው የአንድ እናት ልጆች ወንድምና እህት መሆናቸውን ሳያውቁ የተጋቡት።
ለ20 ዓመታት ገደማ በትዳር የኖሩት እና የአንዲት ሴት ልጅ ወላጅ የሆኑት አድሪያና እና ሊዮናርዶ ከክስተቱ በኋላ ስለትዳራቸው ሲጠየቁም እናቸውን እንደማይወቀሱ እና በትዳራቸው እንደሚቀጥሉ አስውቀዋል።
ጥንዶቹ ከህረተሰቡ ውግዘት እንደሚደርስባቸው ቢረዱም አብረው ለመኖር መወሰናቸው ግን በይፋ ተናግረዋል።
ይህ ሁኔታ በእናንተ ላይ ቢከሰት ምን ዓይነት ወሳኔ ትወስኑ ነበር.....??
ኮሜንት ላይ ብታካፍሉኝ...😍🙏