Fasilo HD

Fasilo HD Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fasilo HD, Computer Company, Addis Abeba, Addis Ababa.

የመግቢያ ውጤቱ እስኪፈተሽ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜ እንዲራዘም የአማራ ትምህርት ቢሮ ጠየቀበ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ወደዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ውጤት ተፈትሾ መተማመኛ ላ...
19/03/2022

የመግቢያ ውጤቱ እስኪፈተሽ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜ እንዲራዘም የአማራ ትምህርት ቢሮ ጠየቀ

በ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ወደዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ውጤት ተፈትሾ መተማመኛ ላይ እስኪደረስ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ጊዜው እንዲራዘም ተጠየቀ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለትምህርት ሚኒስቴር በፃፈው ደብዳቤ ጠይቋል።

የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ እጅግ በጣም ሰፊ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎቻችን ውጤታቸው እንደገና እንዲፈተሸላቸው እያመለከቱ መሁኑን የገለፀው የክልሉ ትምህርት ቢሮ በተጨማሪ በትምህርት አመራሩና በትምህርት ማህበረሰቡ ዘንድም በርካታ ጥያቄዎች እየተነሱ መሆኑን ቢሮው አትቷል። የተማሪዎች ውጤት በአግባቡ ተፈትሾላቸው ተገቢው መተማመን እስኪፈጠር ድረስ የተማሪዎች መግቢያ ቀን ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ቢሮው በደብዳቤ ትምህርት ሚኒስትርን ጠይቋል፡፡

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

ሰበር ዜና❗️ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድና ደብረ ፅዮን ገ/ሚካኤል ከረጀም አመታት በኋላ በስልክ ተገናኙ❗️በኢትዮጵያ የ "ዘ-ኢኮኖሚስት" መጽሔት ወኪል የሆነው ጋዜጠኛ  #ቶም( Tom  G...
19/03/2022

ሰበር ዜና❗️
ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድና ደብረ ፅዮን ገ/ሚካኤል ከረጀም አመታት በኋላ በስልክ ተገናኙ❗️
በኢትዮጵያ የ "ዘ-ኢኮኖሚስት" መጽሔት ወኪል የሆነው ጋዜጠኛ #ቶም( Tom Gardner) እንዲህ ሲል በቲውተር ገፁ ላይ አስፍሯል።
"ከ18ወራት ቡኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ባሳለፍነው ሳምንት ደብረጽዮን እና አብይ በስልክ ተነጋገሩ፣ከመቅረት ማርፈድ ይሻላል።"ብሏል።

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

በዩንቨርስቲ መግቢያ ነጥብ ላይ ምንም አይነት ማሻሻያ እንደማይደረግ ተገለፀ።       የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ሳሙኤል ክፍሌ ( ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ የጸጥታ ችግር አጋጥሞ በ...
18/03/2022

በዩንቨርስቲ መግቢያ ነጥብ ላይ ምንም አይነት ማሻሻያ እንደማይደረግ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ሳሙኤል ክፍሌ ( ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ የጸጥታ ችግር አጋጥሞ በነበረባቸው አካባቢዎች የተገኘው ውጤት ከሌላው ጊዜ የተለየ አለመሆኑን ተናግረዋል።

ዘንድሮ በ43ቱ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከ187 ሺ በላይ ተማሪዎች ይገባሉ ብለዋል።

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ በበኩላቸው በእርማት ወቅት የነበሩ ስህተቶችን በወቅቱ አስተካክለናል፡ የሚሻሻል የነገር የለም ብለዋል።

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

"በዞኑ 6 ትምህርት ቤቶች የተፈተኑ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አላመጡም" የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ  ወሎ ዞን ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ካስፈተኑ 42 ትምህርት ቤቶች በስድስት ...
18/03/2022

"በዞኑ 6 ትምህርት ቤቶች የተፈተኑ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አላመጡም" የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ

ወሎ ዞን ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ካስፈተኑ 42 ትምህርት ቤቶች በስድስት ትምህርት ቤቶች የተፈተኑ 679 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አላመጡም፡፡

ጊራና ፣ ቃሊም፣ ኩል መሰክ፣ ጉርጉር ደብረሮሀ፣ ሀናመኳት ደብረሲና እና ክበበው 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኾናቸው ተገልጿል፡፡

የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ባለሙያ ወይዘሮ ሙሉ አዳነ ዞኑ ከ5 ወራት በላይ ጦርነት ሲካሄድበት በመቆየቱና አሁንም ቀጣናው ሙሉ በሙሉ ሰላሙ ባልተረጋገጠበት ተማሪዎች ለፈተና በቂ ዝግጅት ሳያገኙ ፈተና መውሰዳቸውን አስረድተዋል፡፡

በጦርነቱ ምክንያት ከደረሰው ሥነ ልቦና ጉዳት ሳያገግሙ ተማሪዎች ፈተና መውሰዳቸው ተገቢ አለመኾኑን የገለጹት ወይዘሮ ሙሉ ትምህርት ሚኒስቴር ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ የወሰነው ማለፊያ ነጥብ ይኸንን ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው ብለዋል፡፡

👉በዞኑ 9 ሺህ 710 ተማሪዎች ተፈትነው 3 ሺህ 657 ተማሪዎች ብቻ ናቸው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ማለፊያ ነጥብ ያመጡት።

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

የቋሪት ወረዳ የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ከትምህርት አለም የማግለል ሴራ አጋልጦታል።የአማራ ተማሪዎች በታቀደ መልኩ ከትምህርት አለም እየተገለሉ ስለመሆናቸው እየተነገረ...
18/03/2022

የቋሪት ወረዳ የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ከትምህርት አለም የማግለል ሴራ አጋልጦታል።የአማራ ተማሪዎች በታቀደ መልኩ ከትምህርት አለም እየተገለሉ ስለመሆናቸው እየተነገረ ነው!

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

ሰበር ዜና❗️የኢንጅነር ስመኘው በቀለ አባት ጋሽ በቀለ ከዚህ አለም ድካም ማረፋቸው ተሰማ።ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇https://t.me/Fasi...
18/03/2022

ሰበር ዜና❗️

የኢንጅነር ስመኘው በቀለ አባት ጋሽ በቀለ ከዚህ አለም ድካም ማረፋቸው ተሰማ።

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

የትምህርት ሚኒስተር የላሸቀ ስራ የአማራ ተማሪዎችን በከፍተኛ ቁጥር ከትምህርት ውጭ አድርጓቸዋል።ዳሩ ግን የአማራ ክልል ላይ የታየው ቀውስ ሌሎችም ላይ ተስተውሏል።የተማሪዎችን ውጤት በከፊል ...
18/03/2022

የትምህርት ሚኒስተር የላሸቀ ስራ የአማራ ተማሪዎችን በከፍተኛ ቁጥር ከትምህርት ውጭ አድርጓቸዋል።ዳሩ ግን የአማራ ክልል ላይ የታየው ቀውስ ሌሎችም ላይ ተስተውሏል።የተማሪዎችን ውጤት በከፊል ይመልከቱ!

👉በዋግኽምራ ጋዝጊብላ ወረዳ 229 ተፈትነው ያለፉት 29 ብቻ ናቸው፣

👉በዳባት ወረዳ 1166 ተፈትነው ያለፉት 37ቱ ናቸው፣

👉በምንጃር ወረዳ 350 ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት 5ቱ ብቻ ናቸው፣

👉ሰሜን ወሎ ጋዞ ወረዳ 350 ተፈትነው ወደ ዩንቨርስቲ ያለፉት 5ቱ ብቻ ናቸው፣

👉ሰሜን ሸዋ መንዝ ቀያ ወረዳ ከተፈተኑት 500 ተማሪዎች ያለፉት 30 ብቻ ናቸው፣

👉ደቡብ ወሎ ለገሀዲ ወረዳ 275 ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት 2ቱ ናቸው፣

👉ጃናሞራ ወረዳ 805 ተፈትነው ያለፉት 120 ተማሪ ብቻ ናቸው፣

👉ታች ጋይንት ደቡብ ጎንደር 1720 ተፈትነው ያለፉት ያለፉት 22 ተማሪዎች ብቻ ናቸው፣

👉ሲዳማ ክልል ሎካ አባያ ወረዳ 444 ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት 5ቱ ናቸው፣

👉ጉራጌ ዞን ኤገር ወረዳ ሁሉም ተፈታኞች አላለፉም፣

👉ከፋ ዞን ገዋታ ወረዳ ካሉት 6 ት/ቤቶች አንድም ያለፈ የለም።

ለፈጣንና ለሀቀኛ መረጃዎች ቤተሰባችን ይሁኑ!
የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/FasilAmhara

የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ👇

https://www.facebook.com/110194134211057/posts/421046496459151/?substory_index=0&app=fbl

ዝርዝር መረጃዎችን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ👇

https://www.youtube.com/channel/UC5uxO6rNeYuNCcGXgM2gQHA

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fasilo HD posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share