Abraham Dagne

Abraham Dagne Hi, I'm Abraham Dagne! I'm a Website developer and a lover of philosophy and programming and coding.

__ጢያ ትክል ድንጋይ ___******************* -------ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ -------* ከ አርባ በላይ በላያቸዉ የተለያዩ ቅርፆች ያሉባቹ ትክል ድንጋዮች ናቸዉ፤* የ ወሬ ...
10/08/2021

__ጢያ ትክል ድንጋይ ___
*******************
-------ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ -------

* ከ አርባ በላይ በላያቸዉ የተለያዩ ቅርፆች ያሉባቹ ትክል ድንጋዮች ናቸዉ፤

* የ ወሬ ዘመን በስራ ዘመን ሲተካ ስለ መካከለኛዉ ዘመን የኢትዮጵያ ነገስታት እና ሕዝብ ተጨማሪ አዲስ ታሪክ የምናዉቅበት ቋሚ ማስረጃ ነዉ፤

* በአቅራቢያዉ የአንፋር ማርያም ጥንታዊ ገዳም መኖሩን ልብ ይሏል፤

10/08/2021

"መንጋውን ንብ ለመያዝ ሠራተኛውን ንብ በሙሉ ማሳደድ ሳይሆን ዘዴው አውራውን መያዝ ነው።"ከሰንፔር ግድግዳው እልፍኝ ለማደርና የውስጡን ምሥጢራት ለማግኘትም መፍትሔው ቁልፉን መቀጥቀጥ ሳይሆን መፍቻውን ከያዘው ፈልጎና ጠይቆ ማግኘት ነው።ገነት ለመግባት መፍትሔው ጉልበት ማፈርጠም ሳይሆን መልካም መሥራት ነው፤በጉልበት ቢሆን ኑሮ እስክንድር ጠቢብ በአሞራ ፈረሱ ዘው ብሎ በገባ ነበር።
አስተዋይ ዓይነ ልቦች ከተከለሉ ቀንም ሌሊትም ጨለማ ናቸው።ከበሩ ደግሞ ሌሊቱም ቀኑም ብርሃን ናቸው።ሰው ጥንትም ሆነ ዛሬ የሚሸወድ ከተሰጠውና በቀላሉ ከሚያገኘው ይልቅ ግብ ግብ መግጠሙና ዙሪያ ጥምጥም ጉዞውን መምረጡ ነው።ቃኤል አቤል ወንድሙን በበቀል ገድሎ ቆንጆ ሚስት ለማግኘት ከመሞከር ይልቅ የአምላኩንና የአባቱን ፈቃድ ቢከተል ኑሮ መፍትሔ በኖረውና የኖድ ሽፍታ የምድር ተቅበዝባዥ ሁኖ ባልቀረ ነበር። ቁልፍ ካለ መፍቻም አለ።ካለመፍቻም የሚቆለፍ በር የለም፤አይኖርምም።ሁለቱም በእጅህ አሉ፤ካልታየህ ከያዘው መጠየቅና ፈልጉ ማግኘት ነው።ሰዶ ማሳደድ ፣ መፍቻ ጥሎ ቁልፍ ለመስበር መታገል ሁለተኛ እዳ ጥበብ ሳይሆን ከራስ መጣላት ነው።"እሳትና ውሃ ቀርቦልሃል፤እጅህን ወደ መረጥከው አስገባ።"...

፠ሰማያዊ መፍቻ

ስንፍናን ማሸነፍ!ሮኬት ወደ ህዋ ሲሄድ አብዛኛውን ጉልበት የሚጨርሰው እስኪነሳ ነው፤ የመሬትን ስበት አሸንፎ በሚገርም ፍጥነት ከፍ ማለት ከጀመረ በኋላ ያንን ፍጥነቱን ማስጠበቅ ቀላል ነው።
09/08/2021

ስንፍናን ማሸነፍ!

ሮኬት ወደ ህዋ ሲሄድ አብዛኛውን ጉልበት የሚጨርሰው እስኪነሳ ነው፤ የመሬትን ስበት አሸንፎ በሚገርም ፍጥነት ከፍ ማለት ከጀመረ በኋላ ያንን ፍጥነቱን ማስጠበቅ ቀላል ነው።

 #እርሳስ፦ በጣም ይቅርታ... #ላጵስ፦ ለምኑ? ምንም ያጠፋኸው ስህተት እኮ የለም #እርሳስ፦ ይቅርታ!! በጣም ጎድቼሀለው ሁሌ እኔ በተሳሳትኩ ጊዜ እኔን ለማረም ስታጠፋኝ አንተ ደግሞ እያነ...
01/08/2021

#እርሳስ፦ በጣም ይቅርታ...
#ላጵስ፦ ለምኑ? ምንም ያጠፋኸው ስህተት እኮ የለም
#እርሳስ፦ ይቅርታ!! በጣም ጎድቼሀለው ሁሌ እኔ በተሳሳትኩ ጊዜ እኔን ለማረም ስታጠፋኝ አንተ ደግሞ እያነስክ እየመጣህ ነው
#ላጵስ፦ አዎ ትክክል ነህ..ግን አስቤውም አላውቅም ተመልከት...እኔ ይህንን የማደርገው አንተን ለመርዳት ነው አንተን ከስህተትህ ለማረም ነው በርግጥ አንድ ቀን እንደምጠፋ አስባለሁ....በእውነቱ በስራዬ በጣም ደስተኛ ነኝ ስለዚህ...አትዘን ያንተን ሀዘን ማየት አልፈልግም
"የአንተ/ቺ እናት እና አባት ማለት ላጵስ ናቸው እኛ ልጆቻቸው ደግሞ እርሳስ ነን ሁሌም ስናጠፋ እኛን ሲያርሙን እኛ ደግሞ ምክራቸውን ወደ ጎን ከተውን ልባቸውን በቀላሉ እየጎዳን የኛን ጥሩ ነገር ሳያዩ እድሚያቸው ሊያልፍ ይችላል ስለዚህ እኛም የዋሉልን ውለታ ስላለ እሱን ለመክፈል መዘጋጀት ይጠበቅብናል
ፈጣሪ ይስጥልን...
🙏አሜን🙏

ስድስቱ አይነ-ስውራን እና ዝሆኑምንም እንኳን ሁሉም አይነ-ስውር ቢሆኑም፡ የማወቅ ጉጉታቸው የበረታ የሆነባቸው፡  ስድስት የኢንዶስታን ነዋሪዎች፡ በመንደራቸው በኩል የሚያልፈውን ዝሆን ”ለማየ...
01/08/2021

ስድስቱ አይነ-ስውራን እና ዝሆኑ

ምንም እንኳን ሁሉም አይነ-ስውር ቢሆኑም፡ የማወቅ ጉጉታቸው የበረታ የሆነባቸው፡ ስድስት የኢንዶስታን ነዋሪዎች፡ በመንደራቸው በኩል የሚያልፈውን ዝሆን ”ለማየት“ በህብረት መጡ፤ የእውቀት ጥማታቸውንም ለመቁረጥ ቸኮሉ።

ከመሀከላቸው አንዱ ወደ ዝሆኑ ጎን ተጠግቶ ዳሰሰው፤ ለመናገርም ቀደመ፤ እንዲህም አለ፦

”የዝሆን ፍጥረት እንደ ግድግዳ ነው!“

ሁለተኛውም ቀጠለ። ወደ ዝሆኑም ተጠጋ፤ ጥርሱንም ዳሰሰ። እንዲህም አለ፦

”የዝሆን ፍጥረት ልክ እንደ ጦር መሆኑ አያጠራጥርም!“

ሶስተኛውም ተራ ደረሰው፤ እንስሳውንም ዳሰሰው። ከኩንቢውም ደረሰ። መናገርም ጀመረ፤ እንዲህም አለ፦

”ዝሆን እንደ እባብ ያለ ፍጥረት ነው!“

አራተኛውም ተከተለ፤ እጁንም ዘረጋ። ከዝሆኑ እግርም ደረሰ። እንዲህም አለ፦

”የዝሆን ፍጥረቱ፡ ልክ እንደ ዛፍ ነው ቁመቱ!“

የዝሆኑን ጆሮ የመዳሰስ አጋጣሚ የደረሰውም አምስተኛው ባለተራ ሀሳቡን ደመደመ። እንዲህም አለ፦

”ዝሆን ከማራገቢያ ምንም አይለይም!“

የመጨረሻውም ተራ ደረሰው። የዝሆኑ ጭራም ከእጁ ገባ። እንዲህም አለ፦

”ዝሆን እንደ ገመድ ያለ ነገር ነው!“

ከዚህ ሁሉ በኋላም በአይነስውሮቹ ዘንድ ታላቅ ክርክር ሆነ። በከፍተኛ ጩኸትም፡ ረጅም ሰዓት የፈጀ ጭቅጭቅ ሆነ፤ ስምምነትም ጠፋ።እያንዳንዳቸው በከፊል ልክ ቢሆኑም፡ ሁሉም ተሳስተው ነበር!

እስኪ ከኛ ውስጥ መንፈሱ ያልታወረ ማን ነው?የማያልቀው ክርክራችንስ ከዚሁ አይደለምን?

፨፨፨፨፨፨፨ኢትዮጵያ ፨፨፨፨፨፨፨ዛሬ ሀገርህን መታደግ የፈለግክ በጎራዴ አይደለም ሀገርህን የምታድነው። የተሰረቀውን ጭንቅላትህን በማስመለስ እንጂ የሀገርህን ንቀህ የሰው እየተመኘህ እንዴት ይ...
15/06/2021

፨፨፨፨፨፨፨ኢትዮጵያ ፨፨፨፨፨፨፨
ዛሬ ሀገርህን መታደግ የፈለግክ በጎራዴ አይደለም ሀገርህን የምታድነው። የተሰረቀውን ጭንቅላትህን በማስመለስ እንጂ የሀገርህን ንቀህ የሰው እየተመኘህ እንዴት ይህንን መሰል ጀግና ለማወደስ አፍህ እስ አለህ? የሀገርህን መመስረት ታርክ ማታውቅ እንዴት ስለሀገርህ በጎ ነገር ለመናገር አፍህ ተከፈተ ወገኔ ሆይ የአባቶችህን እውቀት መርምር በጥበባቸውም ተራቀቅበት እራስህንም አገርህንም ከቁራኛንት አድን።

ዛሬ ያለ ጦር መሳሪያ እኔ እና አንተን አሸንፈውናል። በአባቶቻችን እውቀት ብቻ ሀገራችንንም እራሳችንንም ከቁራኛነት እናስለቅቅ።

የራሱን ንቆ የሰው ሚያከብር አሽቃቫጭ እንጂ አዋቂ አይባልም። ራሱን ራቁት ቆሞ ሰው ቢያለብሥ እውነት እሱ ለጋስ ነው?

06/05/2021

ተስፋ ሊያስቆርጥህ የጨከነን ኋይል አንተም ተስፋ ላለመቁረጥ ጨክነህ ነው የምትሻገረው ፤ የምታሸንፈው !
----------------//////---------------

 #የሚናገር መፅሀፍ *እንደ እባብ ብልህ መሆን ማለት ምን ማለት ነው? ሰሞኑን ይሄንን መፅሀፍ እያጠናሁ -እያመነጀኩ ነው ስለእባብ ጥበብ እየተደነኩ ለህይወቴ እየተማርኩ.... "ነዋሪነትህ ዝ...
04/05/2021

#የሚናገር መፅሀፍ *እንደ እባብ ብልህ መሆን ማለት ምን ማለት ነው? ሰሞኑን ይሄንን መፅሀፍ እያጠናሁ -እያመነጀኩ ነው ስለእባብ ጥበብ እየተደነኩ ለህይወቴ እየተማርኩ.... "ነዋሪነትህ ዝብርቅርቁ በወጣ ድሀ አገር ከሆነ ግራ በተጋባባት ስፍራ ጥቂት ስርዓት ለማስፈን ስትሞክር በሚገጥምህ ተቃውሞ ትገረማለህ። ስለምታመጣቸው ሀሳቦች ሰዎች ይነሱብሀል ይጠሉሀል! ለመረዳት በመሞከርህ የሚከብድ ክፉ ስም ይሰጥሀል! ....በበርካታ ድሀ አገሮች ሱቆች በየስፍራው የመኪና ሽያጭ በየስፍራው ፣ የተበላሹ መኪናዎች በዋና መንገዶች በዋና መንገዶች ላይ ቆመው የቆሸሹ ቱቦዎች እና ማጠራቀሚያዎች በፕላስቲክ እና በቆሻሻ ቱቦዎች እና ማጠራቀሚያዎች አፕላስቲክ እና በቆሻሻ ታጭቀው ይገኛሉ ይህ ሁሉ ተመልካች የለውም! ህዝብ ብቃት የሌላቸውን ሰዎች መሪ አድርጎ እስከመረጠ ድረስ ይህ ግራ የአጋባ ሁናቴ ይቀጥላል! " ገፅ 62

02/05/2021

ዘመን የማይሽረው ፍቅር በእውነት በመስቀል ተሰቅሎ ቆስሎ እና ሞቶ ላዳነን ሞቶም አልቀረ በትንሳኤ ላረገበት ቀን ላደረሰን ጌታ በእውነት ስሙ የተመሰገነ ይሁን እንኳን ለትንሳኤው አደረሣቹ አደረሠን በእውነት ለእኛ ሰው የሆነ አምላክ በፅድቅ ስራው አፍረን እርሱ በስራችን ሳያፍርብን ለዚህች እለት ለዚች ሰአት አብቅቶናልና ስሙ የተመሰገነ ይሁን
ክርሰቶስ ተንስአ እምዉታን
በአብይ ሀይል ወስልጣን
አሰሮ ለሴይጣን
አጋዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዜሰ
ኮነ ፍስሀ ወበ ሰላም በእውነት በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን አስተውሉ ይህ ዘመን የደስታ ዘመን አደለምና በንስሀ ታጠብን ለቅድስና የምንሮጥበት ነውና ሁላችንም ለነፍሳችን ዋጋ እንስጥ ቸር ዘመን ፈጣሪ ያምጣልን እንደ ቸርነቱ እርሱም ይምጣልን
አሜን ማራናታ ።

 #እሑድ ማለዳ ላይ ብዙ ሴቶች ( መግደላዊት ማሪያም ፣ ዮሐና ፣ ሰሎሜ እና የያዕቆብ እናት ማርያም) ወደ መቃብሩ ሄደው መግቢያውን የሸፈነው ትልቁ ድንጋይ እንደተገለበጠ አገኙ ፡ አንድ መል...
01/05/2021

#እሑድ ማለዳ ላይ ብዙ ሴቶች ( መግደላዊት ማሪያም ፣ ዮሐና ፣ ሰሎሜ እና የያዕቆብ እናት ማርያም) ወደ መቃብሩ ሄደው መግቢያውን የሸፈነው ትልቁ ድንጋይ እንደተገለበጠ አገኙ ፡ አንድ መልአክ አስታወቀ፡፡
//
በመላው አለም ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳዔ በሰላም አደረሳችሁ‼
//
መልካም በዓል!!

እንኳን ለብርሃነ ስቅለቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን
30/04/2021

እንኳን ለብርሃነ ስቅለቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

Address

Addis Ababa
0000

Telephone

+251909339775

Website

https://abrahamdagne.com/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abraham Dagne posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Abraham Dagne:

Share